በአዲስ አበባ በሚካሄደዉ የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ላይ 35 ፕሬዝዳንቶችና 4 ጠቅላይ ሚኒስትሮች ይሳተፋሉ

ቀጣዩን የአፍሪካ ኅብረት ፕሬዝዳንትነት ኮሞሮስ ከሴኔጋል ትረከባለች።

Amb Alem.jpg

Ambassador Meles Alem, Spokesperson of the Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia. Credit: MFAE

በአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ላይ የ51 አገራት ልዑካን ቡድኖች እንደሚሳተፉ ታዉቋል፡፡

በመድረኩ ላይ 35 ርዕሰ-ብሔሮች፣ አራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች፣ 11 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ 13 ቀዳማዊ እመቤቶችና 10 የዓለም አቀፍ ድርጅት ኃላፊዎች ይታዳማሉ ተብሏል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ከነገ ጀምሮ 36ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ መካሄድ ይጀምራል፡፡

ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ጉባኤው የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ጉዳይ ላይ በስፋት እንደሚመክር ተናግረዋል።

በጉባኤው የፀጥታ ምክር ቤት ማሻሻያ እና የተለያዩ የሕግ ሰነዶች ይጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ቀጣዩን የአፍሪካ ኅብረት ፕሬዝዳንትነት ኮሞሮስ ከሴኔጋል ትረከባለች ብለዋል።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service