Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የአውስትራሊያ የፓፕዋ ኒው ጊኒ የውጭ ዕርዳታ 'ለብሔራዊ ጥቅም ፋይዳ' እንዳለው ገለጡ

በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ እሥራኤላውያን የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን ወግ አጥባቂ መንግሥት የድንጋጌ ለውጥ ተቃውመው ሰልፍ ወጡ

Anthony Albanese attends a welcome ceremony in Wewak during his visit to Papua New Guinea earlier this week.jpg

Anthony Albanese attends a welcome ceremony in Wewak during his visit to Papua New Guinea earlier this week. He is the first Australian leader to visit the country since 2018. Credit: AAP / Prime Minister's Office/Anthony Albanese

የጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዝን የሁለት ቀናት ጉብኝት ተከትሎ የአውስትራሊያንና ፓፕዋ ኒው ጊኒንን የሁለትዮሽ ግንኙነት በይበልጥ ለማጠናከር ተጨማሪ ዕቅድ ተይዟል።

አውስትራሊያ ለፓፕዋ ኒው ጊኒ የውጭ ዕርዳታዋን ያጠናከረች ሲሆን፤ ያም "ለአውስትራሊያ ብሔራዊ ጥቅም" ከፍ ያለ ፋይዳ እንደሚኖረው አቶ አልባኒዚ አመላክተዋል።

የአውስትራሊያ ተገማች 2022-23 የውጭ ዕርዳታ በጀት $500 ሚሊየን ሲሆን፣ ለፓፕዋ ኒው ጊኒ የሚውለው ዕርዳታ ለሴቶች አመራር ብቃት ማዳበሪያ፣ ለትምህርት ማስፋፊያና የጤና ሥርዓት ማጠናከሪያ እንደሚውል ተገልጧል።

እሥራኤል

በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ እሥራኤውያን የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን የሕግ ማሻሻያ ትልም ተቃውመው የአደባባይ ሰልፍ አካሂደዋል።

ኔታንያሁና ወግ አጥባቂ ሃይማኖታዊ ብሔረተኛ ቅንጅት አጋሮቻቸው የመንግሥትን ሶስትዮሽ ቅርንጫፍ 'ሚዛን ለማስጠበቅ' በሚል አስባብ

የጠቅላይ ፍርድ ቤትን ውሳኔ ለመቀልበስ የሚያስችል ረቂቅ ድንጋጌ ነድፈዋል።

ረቂቅ ድንጋጌው የፍትሕ ሥርዓቱን ነፃነት ያሽመደምዳል፣ ሙሰኝነትን ያስፋፋል፣ የአናሳ ወገኖችን መብቶች ይሸርፋል የሚሉ ብርቱ ትችቶችን ከወዲሁ አስከትሏል።  

የተቃውሞ ሰልፉን ላይ ከተገኙት የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች አንዱ የሆኑት ጂል ሊብርውስኪ ስለ ምን ለተቃውሞ ሰልፍ አደባባይ እንደወጡ ሲናገሩ " ለተቃውሞ ሰልፍ የወጣሁት ዲሞክራሲያችንና የፍትሕ ተቋማችንን ከመነጠቅ ለመከላከል ነው። ጠንካራና ነፃ የፍትሕ ሥርዓት ያሻናል፤ መንግሥታችን ግና ሊከላው ይፈልጋል። ፕሬዚደንቱን በማናገር ያ ዕውን እንዳይሆን እንዲያደርጉና ከእኛ ወገን እንዲቆሙ ለማድረግ እየጣርን ነው" ብለዋል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now