Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

የዩናይትድ ስቴትስና የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በአንኳር ጉዳዮች ላይ ተነጋገሩ

ትናንት ምሽት አዲስ አበባ የገቡት የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ተወያይተዋል።

Ethiopia US Diplomacy.jpg

US Secretary of State Antony Blinken (2nd L) meets with Ethiopian Deputy Prime Minister and Foreign Minister Demeke Mekonnen (3rd R) in Addis Ababa, Ethiopia, on March 15, 2023. Credit: TIKSA NEGERI/POOL/AFP via Getty Images

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር ተወያይተዋል

በውይይታቸው ወቅት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

ብሊንከን በቀጣይ ከሰብዓዊ ድርጅቶች እና ከከሲቪክ ተቋማት ጋር በሰብዓዊ ዕርዳታ ስርጭት፣ በምግብ ዋስትና እና በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ እንደሚነጋገሩ የሚጠበቅ ሲሆን፤ በተጨማሪም ከአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት ጋር እንደሚገናኙ ተነግሯል።

አቶ ብሊንከን ወደ ኢትዮጵያና ኒጀር ከማቅናታቸው በፊት የአፍሪካ አገራት በምህብ ዋስትና፣ የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ፣ ሉላዊ ጤና፣ ሰብዓዊ መብቶችና ሰላም ሁነኛ ሽርካዎች መሆናቸውን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የዩናይትድ ስቴትስ አቻቸውን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውን ገልጧል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now