የሁለቱም ወገን የተርክዬ ፕሬዚደንታዊ ዕጩዎች አሸናፊነታቸው ቢገልጡም ምርጫው ዳግም ሊካሔድ ይችላል

ቪክቶሪያ ውስጥ የናዚ ሰላምታ እንዲታገድ ጥያቄ ቀረበ

Türkiye Election.jpg

Turkiye awaits the results of the general election. Credit: ADEM ALTAN/AFP via Getty Images

የተርክዬ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አሸናፊ ውጤት በይፋ በምርጫ ኮሚሽን በኩል ባይነገረም ከሁለቱም ዕጩ ፕሬዚደንቶች በኩል አሸናፊነታቸውን እየገለጡ ነው።

እስካሁን 80 ፐርሰንት ያህል የመራጮች ድምፅ ተቆጥሯል።

ፕሬዚደንት ኢርዶጋንና ተቀናቃኛቸው ከማል ኪሊችዳሮሉ በየፊናቸው አሸናፊነታቸውን ቢገልጡም ሁለቱም ከ45 ፐርሰንት የዘለለ ድምፅ አላገኙም።

 ከሁለቱ ዕጩ ፕሬዚደንቶች አንዳቸው 50 ፐርሰንት ላይ ካልደረሱ ሜይ 28 ዳግም ምርጫ ይካሔዳል።

የፕሬዚደንት ኢርዶጋን ፓርቲ ቃል አቀባይ አቶ ኢርዶጋን በምርጫው ውጤት እየመሩ ቢሆንም፤ የምርጫ ኮሚሽኑን ይፋዊ ወጤት እንደሚያከብሩ ተናግረዋል።

 
የናዚ ሰላምታ

በሳምንቱ መጨረሻ ላይ በቪክቶሪያ ፓርላማ ፊት ለፊት የተካሔደውን ፀረ ኢሚግሬሽን ሰልፍ ተከትሎ የቪክቶሪያ መንግሥት የናዚ ሰላምታን በአፋጣኝ እንዲያግድ ጥያቄዎች ቀርበዋል።
 
የቪክቶሪያ ፖሊስ ቅዳሜ ዕለት በናዚ ሰላምታ ሰጪዎችና ተፃራሪዎች መካከል በተካሔደው ግጭት አለመደስቱን ገልጧል።

 ፖሊስ ግጭቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል እንደቻለና ጥቁር ለብሰው ከነበሩት 20 ያህል የተቃውሞ ሰልፈኞች ውስጥ ሁለቱን ለእሥር መዳረጉን አስታውቋል።

በዲከን ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶ/ር ጆሽ ሮዝ፤ የናዚ ሰላምታን ለማገድ ሂደቱ ረጅምና አዋኪ እንደሚሆን አመላክተዋል።

 




Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service