ሌበር ፓርቲ ለሜዲኬይር ማጠናከሪያ ተጨማሪ $970 ሚሊየን ዶላርስ መደበ

*** ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን በዛሬው የይፋ አገራዊ ምርጫ ዘመቻ መክፈቻቸው ላይ ተያያዥ የጡረታና የቤት ፖሊሲ ሊያስታውቁ ነው

News

Australian Opposition Leader Anthony Albanese (L) and Australian Prime Minister Scott Morrison (R). Source: SBS

የሌበር ፓርቲ በቅዳሜው አገራዊ ምርጫ ለመንግሥትነት ከበቃ $970 ሚሊየን ዶላርስ ለሜዲኬይርና የአካባቢ ጤና መደጎሚያ እንደሚያውል አስታወቀ።

ከበጀቱ ውስጥ $750 ሚሊየን ለሜዲኬይር ግብረ ኃይል ማጠናከሪያ፣ ሕመምተኞች ሐኪሞች ዘንድ የተሻለ ተደራሽነት እንዲኖራቸው፣ ሆስፒታሎች ላይ ያለውን ጫና ለመቀነስ፣ ውስብስብና ስር የሰደዱ ሕመሞችን በተሻለ ሁኔታ ለማከም የሚውል ይሆናል።   

 የመኖሪያ ቤት ፖሊሲ

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ ብሪስበን ላይ በይፋ በሚከፈተው የሊብራል ፓርቲ አገር አቀፍ ምርጫ መክፈቻ ላይ የቤት ፖሊሲያቸውን ያስታውቃሉ። 

በአዲሱ ፖሊሲ መሠረት 1.3 ሚሊየን ያህል ዕድሜያቸው ከ55 በላይ የሆኑ ሰፋፊ ቤቶቻቸውን ሸጠው ወደ አነስተኛ ቤት በመቀየር እስከ $300,000 በግለሰብ ደረጃ ወደ ጡረታ አበላቸው መጨመር ይችላሉ። 

ይህም ወጣት ቤተሰቦች ሰፋፊ ቤቶችን ለመግዛት እንዲችሉ የሚያግዝ መሆኑ ተጠቅሷል።  

 

 

 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service