የአውስትራሊያ ሊብራል ፓርቲ አገራዊ የምርጫ ዘመቻውን በይፋ ጀመረ

*** አቶ ሞሪሰን በመጀመሪያው የሶስት ዓመት ተኩል ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ወቅት ገና "እየተሟሟቁ" እንደሁ ጠቅሰው፤ አውስትራሊያውያን ዳግም እንዲመርጧቸው ጠይቀዋል።

News

Prime Minister Scott Morrison at the Liberal Party campaign launch on Day 35 of the 2022 federal election campaign, at the Brisbane Convention Centre. Source: AAP

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ እኩለ ቀን ላይ የሊብራል ፓርቲን ይፋ የአገራዊ ምርጫ ዘመቻ ብሪስበን ከተማ ከፍተዋል። 

አውስትራሊያ ከወረርሽኙ አልፋ አንገቷን ቀና አድርጋ ለመቆም መብቃቷንም ጠቅሰዋል። 

የምርጫ ዘመቻ መክፈቻ ስብሰባው በተካሔደብት የብሪስበን ጉባኤ ማዕከል የቀድሞ የሊብራል ጠቅላይ ሚኒስትራት ጆን ሃዋርድና ቶኒ አበት ተገኝተዋል።

News
Former prime minister Tony Abbott (L), Jeanette Howard (C), and husband former prime minister John Howard (R). Source: AAP

ሆኖም ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የተኳቸው የሊብራል ጠቅላይ ሚኒስትር ማልከም ተርንቡል በሥፍራው አልተገኙም። 

ከቶውንም አቶ ተርንቡል ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ ይፋ ያደረጉትን ከጡረታ አበል ተቀማጭ ላይ ወስዶ ቤት የመግዛት ፖሊሲ "እብደት የተመላው ዕሳቤ" ሲሉ አክርረው ተችተዋል።

News
Malcolm Turnbull, former Australian Prime Ministel. Source: Getty

በአዲሱ ፖሊሲ መሠረት 1.3 ሚሊየን ያህል ዕድሜያቸው ከ55 በላይ የሆኑ ሰፋፊ ቤቶቻቸውን ሸጠው ወደ አነስተኛ ቤት በመቀየር እስከ $300,000 በግለሰብ ደረጃ ወደ ጡረታ አበላቸው መጨመር ይችላሉ። 

ይህም ወጣት ቤተሰቦች ሰፋፊ ቤቶችን ለመግዛት የሚያስችል መሆኑ ተነግሯል።

አቶ ሞሪሰን መንግሥታቸው ዳግም ከተመረጠ የመጀመሪያ ቤት ገዢዎች ከጡረታ አበል ተቀማጫቸው እስከ 50 ሺህ ዶላርስ ወጪ በማድረግ ለቤት ግዢ የቅድሚያ ተቀማጭ ክፍያ ማድረግ እንዲችሉ የሚፈቅድ መሆኑንም አስታውቀዋል።  

የቀድሞው የሌበር ጠቅላይ ሚኒስትር ፓል ኪቲንግ ግና "ሊብራሎች ከመነሻው የጡረታ አበል ተቀማጭ ሥርዓትን ይጠላሉ። ሠራተኛ አውስትራሊያውያን በጡረታ ዘመናቸው ከመንግሥት ነፃ ሆነው ሃብት እንዳይኖራቸው ይቃወማሉ" በማለት የሊብራል ፓርቲ ፖሊሲ ላይ ነቀፌታ ሰንዝረዋል። 

News
A general view as Australian Prime Minister Scott Morrison addresses the crowd at the Liberal Party election campaign launch on May 15, 2022 in Brisbane. Source: Getty

አቶ ሞሪሰን በመጀመሪያው ዙር የሶስት ዓመት ተኩል ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ገና "እየተሟሟቁ" እንደሁ ጠቅሰው አውስትራሊያውያን ዳግም እንዲመርጧቸው ጠይቀዋል። 

ተቀናቃኛቸው የሌበር ፓርቲ መሪ አቶ አንቶኒ አልባኒዚም ብሪስበን ከተማ ተገኝተው ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገዋል።

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now