"ግርማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ የጤና ዕክል እንኳ ገጥሟቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከልባቸው አልጠፋም፤ የጎንደር ድል በዓል እንዲከበር ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል" የዘውድ ም/ቤት

"ንጉሥ ቻርልስ [ሳልሳዊ] ግርማዊት ንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ስለነበራቸው ዘላቂ ወዳጅነት ጠንቅቀው ያውቃሉ። ስለዚህም፤ እኛም የተወደዱትን እናታቸውን ሲያጡ እንደ ቤተሰብ የሐዘናቸው ተካፋይ ነን" የኢትዮጵያ የዘውድ ምክር ቤት

Queen Elizabeth II and Prince Philip with Emperor Haile Selassie I of Ethiopia (1892 - 1975).jpg

Queen Elizabeth II and Prince Philip with Emperor Haile Selassie I of Ethiopia (1892 - 1975) upon their arrival in Addis Ababa, during a State Visit to Ethiopia, February 1965. Credit: Keystone/Hulton Archive/Getty Images

የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት መስከረም 3, 2015 / ሴፕቴምበር 13, 2022 ባወጣው የሐዘን መግለጫ በዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገለጠ።

በዘውድ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ልዑል ኤርሚያስ ሣህለ ሥላሴ ኃይለ ሥላሴ አማካይነት ሐዘኑን የገለጠው ምክር ቤት፤ ንግሥት ኤልሳቤጥ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራቸውን ጥልቅ ግንኙነትና ያበረከቷቸውንም አስተዋፅዖዎች ዋቤ ነቅሶ በማመላከት ነው።

አያይዞም፤ በንግሥቲቱ ሕልፈት ጥልቅ ሐዘን የገባው ቢሆንም፤ በሕይወት ሳሉ ለኢትዮጵያና ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስላሳዩት ወዳጅነትና ዘላቂ ግንኙነት "በኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት ስም ልንዘክራቸው እንወዳለን" ብሏል።

CCE.jpg
The Crown Council of Ethiopia. Credit: CCE
አክሎም፤ ንግሥት ኤልሳቤጥና አፄ ኃይለ ሥላሴ እርስ በርሳቸው የሚተማመኑና አንዳቸው ላንዳቸው አገር ሕዝብ ደህንነት ተጨናቂዎች እንደንበሩም አመላክቷል።

የንግሥት ኤልሳቤጥን የኢትዮጵያ ጉዞ አስመልክቶም "ንግሥት ኤልሳቤጥ ኢትዮጵያን የጎበኙት አፄ ኃይለ ሥላሴን እጅ ለመንሳት፣ የምንወደውን ሕዝባችንን በዓይናቸው ለማየትና ለመጠየቅ እንዲሁም ውብና ለምለም አገራችንን ለመጎብኘት ነበር" ብሏል።

Queen Elizabeth II at the impressive Tissisal Falls.jpg
Queen Elizabeth II at the impressive Tissisal Falls, where the Blue Nile begins, with Emperor Haile Selassie during a royal visit to Ethiopia, February 1965. Credit: Hulton Archive/Getty Images
የዘውድ ምክር ቤቱ መግለጫ " በሁለተኛው የኢጣሊያን ወረራ ጊዜ የንግሥት ኤልሳቤጥ አባት ንጉሥ አፄ ጊዮርጊስ 6ኛው ለአፄ ኃይለ ሥላሴ መሸሸግያ ቦታ እንዲይዙ በመፍቀድ ኢትዮጵያን ጭካኔ ከተሞላው የአምስት አመት የኢጣልያን ይዞታ ነፃ እንድናወጣና ሉዓላዊነታችንን ለሕዝባችን መልሰን እንድናስረክብ የተሰናዳንበትን ሁኔታ አመቻችተዋል" ሲልም የአገረ እንግሊዝና ኢትዮጵያ ወዳጅነት ከሉዓላዊነትና ሙሉዕ ነፃነት ጋር የተቆራኘ ስለመሆኑ ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ልዑል ኤርሚያስ ሣህለ ሥላሴ ኃይለ ሥላሴ የ1967 መስከረም 2 መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ላይ ግድያ በመፈፀሙ ሳቢያ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ላልቻሉ ንጉሣዊ ቤተሰቦች ንግሥቲቱ ድጋፍ በማድረግ ዘላቂ የቤተሰብ ጓደኛና ባውለታ መሆናቸውን እንዳስመሰከሩ ጠቅሰዋል።

አያይዘውም "እኔ በግሌ የንግሥቲቱ ደግትና ቸርነት ተካፋይ ስለነበርኩህ በቅርበት ንግሥቲቱና የብሪታንያ ሕዝብ ለኢትዮጵያውያን ሰለሞናዊ የዘር ሐረግ ተወላጅ ዘመዶቻቸው አለኝታና ሰብሳቢም ጭምር እንደነበሩ ለመገንዘብ ችያለሁ" ብለዋል።


የዘውድ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት፤ ንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ ንግሥት ኤልሳቤጥ ከኢትዮጵያ ጋር ስለነበራቸው ጥልቅ ግንኙነት ጠንቅቀው እንደሚያውቁ አመላክተው "እኛም የተወደዱ እናታቸውን ሲያጡ እንደ ቤተሰብ የሐዘናቸው ተካፋይ ነን" ሲል በምክር ቤቱ ስም የሐዘን ተጋሪነታቸውን ገልጠዋል።

በመጨረሻም "እግዚአብሔር የዳግማዊት ኤልሳቤጥን ነፍስ ይማርልን። ወደ ፈጣሪዎ ስንሸኝዎት ሐዘናችንን የምንገልጸው በዕንባ ነው። ረጅም ዕድሜ ለንጉሥ ቻርልስ 3ኛው ከመልካም ምኞትና ፀሎት ጋር እንመኛለን። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ለዘላለም ይባርክ" ብለዋል።

Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service