'ዲሞክራሲያችንን የሚያጎድፍ'፤ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አምስት የሚኒስትርነት ኃላፊነቶችን በምስጢር ደርበው ይዘው ነበር

የቀድሞዋ የሞሪሰን አገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ካረን አንድሩስ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ከኩክ ምክር ቤት አባልነታቸው እንዲለቁ ጥሪ አደረጉ

Former Prime Minister Scott Morrison .jpg

Former Prime Minister of Australia Scott Morrison. Credit: Mick Tsikas-Pool/Getty Images

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አምስት ሚኒስትሪያዊ ኃላፊነቶችን ደርበው ይዘው እንደነበር ገለጡ።

ስኮት ሞሪሰን ከማርች 2020 እስክ ሜይ 2021 በጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ላይ የጤና፣ ፋይናንስ፣የአገር ውስጥ ጉዳዮች፣ በጅሮንድ፣ ኢነርጂና ሃብቶች ሚኒስትርም ነበሩ።

ትናንት ሰኞ የአውስትራሊያ ጠቅላይ እንደራሴ ስኮት ሞሪሰን ተጨማሪ ሚኒስትሪያዊ ኃላፊነቶችን ቃለ መሐላ ፈፅመው ይዘው እንደነበር ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

 ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የቀድሞው መንግሥት ምስጢራዊና ፓርላማውን ባሳሳተ መልኩ ይመራ እንደነበር ተናግረዋል።

የፋይናንስ፣ በጅሮንድና የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትሮች ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ ኃላፊነቶቻቸውን ደርበው መያዛቸውን እንደማያውቁ ተናግረዋል።

PM Anthony Albanese.jpg
Prime Minister Anthony Albanese. Credit: Brook Mitchell/Getty Images

የቀድሞዋ የሞሪሰን አገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ካረን አንድሩስ ሚኒስትራዊ ኃላፊነታቸው በስኮት ሞሪሰን ተይዞ እንደነበር ያወቁት በዚህ ሳምንት ከሚዲያ ሪፖርት እንደሆነ ጠቅሰው የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ከኩክ ምክር ቤት አባልነታቸው እንዲለቁ ጥሪ አድርገዋል።

አክለውም፤ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ድርጊት ዲሞክራሲን እንደማይታደግና ለአውስትራሊያ ሕዝብም እንደማይበጅ ተናግረዋል።

Karen Andrews.jpg
Former Minister for Department of Home Affairs Karen Andrews. Credit: Tracey Nearmy/Getty Images

በርካታ የሞሪሰን ካቢኔ አባላት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አምስት ተጨማሪ ሚኒስትሪያዊ ስልጣኖችን ደርበው መዛቸውን ገና አሁን ስለመስማታቸው እየተናገሩ ነው።

 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የሚኒስትሮችን የሥራ ኃላፊነት ደርበው በመያዛቸው ቅር ያሰኟቸው ካሉ 'ይቅርታ' ብለዋል።

ይሁንና ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የስኮት ሞሪሰን ድርጊት 'ዲሞክራሲን የሚያጎድፍ ነው' በማለት ሕጋዊ ምክር መጠየቃቸውንና ድርጊታቸው ሕጋዊ እርምጃን የሚያስወስድ መሆኑንና አለመሆኑን ለመለየት በሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ ከፌዴራል መንግሥቱ የሕግ አማካሪ ሕጋዊ ማብራሪያ እንደሚሰጣቸው ገልጠዋል።

Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
'ዲሞክራሲያችንን የሚያጎድፍ'፤ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አምስት የሚኒስትርነት ኃላፊነቶችን በምስጢር ደርበው ይዘው ነበር | SBS Amharic