የአውስትራሊያ ሥራ አጥነት ቁጥር ከ 3.5 ፐርሰንት ወደ 3.7 ፐርሰንት ከፍ አለ።
የአውስትራሊያ ስታቲስቲክ ቢሮ እንዳመለከተው የሥራ ተሳትፎ ከ 66.5 ፐርሰንት በ 0.1 ፐርሰንት ዝቅ ብሏል።
በሪፖርቱ መሠረት 11,500 ሥራዎች ታጥፈዋል፤ አንድ የአውስትራሊያ ዶላር ከ69 የአሜሪካ ሳንቲም በታች ወርዷል።
ባለፈው ወርኃ ዲሴምበር የሥራ አጥነት ቁጥር 3.5 ፐርሰንት የነበረ ሲሆን፤ 14,600 ሥራዎች ታጥፈዋል።
ድምፅ ለፓርላማ
የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ብሔራዊ ፕሮግራም በዚህ ዓመት ሊካሔድ ስለተወጠነው ሕዝበ ውሳኔ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስና ግንዛቤዎችን ለማስጨበጥ ደጋፊ አባላቱ በዚህ ሳምንት መጨረሻ የድርጊት መርሐ ግብራቸውን በይፋ ሊዘረጉ ነው።
የኡሉሩ መግለጫ አቀናባሪዎች በብሔራዊ የድርጊት ሳምንት ውስጥ ቅዳሜ ፌብሪዋሪ 18 በኦንላይና በአካል ተገናኝተው የመረጃ ልውውጥ ውይይቶችን ለማካሔድ ተልመዋል።
የኡሉሩ ውይይት ተባባሪ ሊቀመንበር ፓት አንደርሰን አውስትራሊያውያን በዚህ ዓመት በሚከናወነው ሕዝበ ውሳኔ ስለ ነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ተልዕኮን በውል ተገንዘበው ድምፃቸውን እንዲሰጡ የሚሹ መሆኑን አመልክተዋል።