የአውስትራሊያ ሥራ አጥነት ቁጥር ወደ 3.7 ፐርሰንት አሻቀበ

የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ደጋፊዎች ዓላማና ተልዕኳቸውን አስመልክቶ አውስትራሊያውያንን ግንዛቤ ለማስጨበጥ የድርጊት መርሐ ግብራቸውን በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሊጀምሩ ነው።

A general view of a Centrelink office in Footscray.jpg

A general view of a Centrelink office in Footscray on March 29, 2021, in Melbourne, Australia. Credit: Darrian Traynor/Getty Images

የአውስትራሊያ ሥራ አጥነት ቁጥር ከ 3.5 ፐርሰንት ወደ 3.7 ፐርሰንት ከፍ አለ።

የአውስትራሊያ ስታቲስቲክ ቢሮ እንዳመለከተው የሥራ ተሳትፎ ከ 66.5 ፐርሰንት በ 0.1 ፐርሰንት ዝቅ ብሏል።

 በሪፖርቱ መሠረት 11,500 ሥራዎች ታጥፈዋል፤ አንድ የአውስትራሊያ ዶላር ከ69 የአሜሪካ ሳንቲም በታች ወርዷል።

ባለፈው ወርኃ ዲሴምበር የሥራ አጥነት ቁጥር 3.5 ፐርሰንት የነበረ ሲሆን፤ 14,600 ሥራዎች ታጥፈዋል።

 ድምፅ ለፓርላማ

የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ብሔራዊ ፕሮግራም በዚህ ዓመት ሊካሔድ ስለተወጠነው ሕዝበ ውሳኔ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስና ግንዛቤዎችን ለማስጨበጥ ደጋፊ አባላቱ በዚህ ሳምንት መጨረሻ የድርጊት መርሐ ግብራቸውን በይፋ ሊዘረጉ ነው።

የኡሉሩ መግለጫ አቀናባሪዎች በብሔራዊ የድርጊት ሳምንት ውስጥ ቅዳሜ ፌብሪዋሪ 18 በኦንላይና በአካል ተገናኝተው የመረጃ ልውውጥ ውይይቶችን ለማካሔድ ተልመዋል።

የኡሉሩ ውይይት ተባባሪ ሊቀመንበር ፓት አንደርሰን አውስትራሊያውያን በዚህ ዓመት በሚከናወነው ሕዝበ ውሳኔ ስለ ነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ተልዕኮን በውል ተገንዘበው ድምፃቸውን እንዲሰጡ የሚሹ መሆኑን አመልክተዋል።




Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service