በሳይክሎን ፍሬዲ በተመታችው ማላዊ 190 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ፤ከ60 ሺህ በላይ ለጉዳት ተዳረጉ

ለሥራ አጥ አውስትራሊያውያን በቀን 76 ዶላር ድጎማ እንዲደረግላቸው ጥሪ ቀረበ

SBS Amharic News Podcast World.jfif

Credit: SBS Amharic

በሳይክሎን ፍሬዲ በተጠቃችው ማላዊ የ190 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፤ ቁጥራቸው በቅጡ ያልታወቁ ሰዎች ቆስለዋል፤ የደረሱበት ሳይታወቅ ቀርቷል።

 በአጎራባቺቱ ሞዛምቢክ ውስጥ ተጨማሪ 20 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

የማላዊ መንግሥት እንዳስታወቀው 60,000 ያህል ዜጎች በማዕበሉ ለጉዳት የተዳረጉ ሲሆን፤ 19 ሺህ ቤት አልባ ሆነዋል።

ድጎማ

የአውስትራሊያ ማኅበራዊ አገልግሎት ምክር ቤት በመጪው በጀት አውስትራሊያውያን ከኑሮ ውድነት ጋር እየታገሉ ባሉበት ሁኔታ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎች መደጎሚያ ቅድሚያ ትኩረት እንዲሰጥ አሳሰበ።

የማኅበራዊ አገልግሎት ምክር ቤቱ በአሁኑ ወቅት በቀን $48 ለሚያገኙ የሥራ አጥነት ድጎማ ተቀባዮች ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ ድጎማቸው ወደ $76 በቀን ከፍ እንዲል ጥሪ አቅርቧል።
 
አክሎም፤ መንግሥት የዘንድሮ በጀቱን ይበልጡን አካታችና ለረጅም ጊዜያት የሚዘልቅ መሠረታዊ የማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ እንዲያውል አሳስቧል።

የአውስትራሊያ ማኅበራዊ ምክር ቤት አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካሳንድራ ጎልዲ፤ የአውስትራሊያ የሥራ አጥነት ድጎማ ከምጣኔ ሃብት ትብብርና ልማት አባል አገራት ውስጥ ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።




Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service