Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

በሳይክሎን ፍሬዲ በተመታችው ማላዊ 190 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ፤ከ60 ሺህ በላይ ለጉዳት ተዳረጉ

ለሥራ አጥ አውስትራሊያውያን በቀን 76 ዶላር ድጎማ እንዲደረግላቸው ጥሪ ቀረበ

SBS Amharic News Podcast World.jfif

Credit: SBS Amharic

በሳይክሎን ፍሬዲ በተጠቃችው ማላዊ የ190 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፤ ቁጥራቸው በቅጡ ያልታወቁ ሰዎች ቆስለዋል፤ የደረሱበት ሳይታወቅ ቀርቷል።

 በአጎራባቺቱ ሞዛምቢክ ውስጥ ተጨማሪ 20 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

የማላዊ መንግሥት እንዳስታወቀው 60,000 ያህል ዜጎች በማዕበሉ ለጉዳት የተዳረጉ ሲሆን፤ 19 ሺህ ቤት አልባ ሆነዋል።

ድጎማ

የአውስትራሊያ ማኅበራዊ አገልግሎት ምክር ቤት በመጪው በጀት አውስትራሊያውያን ከኑሮ ውድነት ጋር እየታገሉ ባሉበት ሁኔታ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎች መደጎሚያ ቅድሚያ ትኩረት እንዲሰጥ አሳሰበ።

የማኅበራዊ አገልግሎት ምክር ቤቱ በአሁኑ ወቅት በቀን $48 ለሚያገኙ የሥራ አጥነት ድጎማ ተቀባዮች ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ ድጎማቸው ወደ $76 በቀን ከፍ እንዲል ጥሪ አቅርቧል።

 

አክሎም፤ መንግሥት የዘንድሮ በጀቱን ይበልጡን አካታችና ለረጅም ጊዜያት የሚዘልቅ መሠረታዊ የማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ እንዲያውል አሳስቧል።

የአውስትራሊያ ማኅበራዊ ምክር ቤት አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካሳንድራ ጎልዲ፤ የአውስትራሊያ የሥራ አጥነት ድጎማ ከምጣኔ ሃብት ትብብርና ልማት አባል አገራት ውስጥ ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።


1 min read

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now