የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በ2023 ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ዕርዳታ የሚውል 331 ሚሊየን ዶላር መፍቀዷን ገለጡ

ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር ስላደረጓቸው ውይይቶችና አሜሪካ ስላደረገቻቸው ልዩ ልዩ ድጋፎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከሕወሓት አመራር አባላትም ጋር ተነጋግረዋል።

AB.jpg

US Secretary of State Antony Blinken holds a press conference during his visit to Ethiopia, in Addis Ababa, on March 15, 2023. Credit: TIKSA NEGERI / POOL / AFP) (Photo by TIKSA NEGERI/POOL/AFP via Getty Images

በአፍሪካ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ትናንት ምሽት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መግለጫ ሰጥተዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር ስላደረጓቸው ውይይቶችና አሜሪካ ስላደረገቻቸው ልዩ ልዩ ድጋፎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን አሜሪካ በፈረንጆቹ 2023 በኢትዮጵያ ለሰብአዊ ዕርዳታ ድጋፍ የሚውል የ331 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ መፍቀዷን ይፋ አድርገዋል። አስታውቀዋል። ድጋፉም በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት [US AID]በኩል እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በአዲስ አበባ ተገናኝተው መምከራቸውንም ገልፀዋል ፡ በስም ማንነታቸውን ባያሳውቁም።

ብሊንከን የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭትን ለመፍታት የሠላም ስምምነት ለፈረሙት ሁለቱም ወገኖች አሜሪካ እውቅና እንደምትሰጥና ለተፈፃሚነቱም ሁለቱም አካላት በትኩረት እንዲሰሩ እንዳሰሰቡ አክለዋል።

ብሊንከን እንዳሉት በጦርነቱ የተሳተፈው የኤርትራ ጦር ከአካባቢው እየወጣ መሆኑንም ገልጸዋል።

ስለአጎዋ ዳግም ዕድል ጉዳይ የተጠየቁት ብሊንከን "የሰላም ስምምነቱ ተጠናክሮ ከቀጠለ ኢትዮጵያ ወደ አጎዋ የገበያ እድል ዳግም መመለስ የምትችልበት እድል ሊኖር ይችላል" ሲሉ ገልጸዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ " የሽግግር ፍትህና አገራዊ ምክክሩ" እንዲጠናከር አሜሪካ አስፈላጊውን እርዳታ እንደምታደርግም ተናግረዋል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ]

Share

Published

Updated

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service