ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አወዛጋቢው የመኖሪያ ቤት ፖሊሲያቸው የቤቶች ዋጋ ንረትን አያስከትለም ብለው እየተከራከሩ ነው

***የአውስትራሊያ ግሪንስ ፓርቲ ዛሬ ሰኞ ምሽት የ173 ቢሊየን ዶላርስ ትልም ይፋ የምርጫ ዘመቻውን ይከፍታል።

News

Aerial view of construction work and housing in Western Sydney on November 13, 2017 in Sydney, Australia. Source: Getty

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የመጀመሪያ ጊዜ ቤት ገዢዎች ከጡረታ አበል ተቀማጫቸው ላይ 40 ፐርሰንት - እስከ $50,000 ወጪ ማድረግ እንዲችሉ የሚፈቅደው  የፓርቲያቸው የመኖሪያ ቤት ፖሊሲ የቤት ዋጋ ንረትን አያስከትልም ሲሉ እየተከራከሩ ነው።  

የጡረታ አበል ሚኒስትር ጄን ሂዩም ግና ዛሬ ጠዋት በሰጡት መግለጫ ፖሊሲው የአጭር ጊዜ የቤቶች ዋጋ ንረትን ሊያስከትል እንደሚችል አምነዋል።

ይሁንና አቶ ሞሪሰን በዕድሜ የገፉ አውስትራሊያውያን ትላልቅ ቤቶቻቸውን ሸጠው ከሽያጩ እስከ $300,000 ወደ ጡረታ አበላቸው እንዲጨምሩ የሚፈቅደው ፖሊሲ የቤቶች የዋጋ ንረት እንዳያሻቅብ ይረዳል ሲሉ ተከራክረዋል። 

አቶ ሞሪሰን የመኖሪያ ቤት ፖሊሲያቸው የገበያ ሁኔታ አመላካች ሞዴል ተሠርቶለት እንደሁና ሞዴሉንም ይፋ ያደርጉ እንደሁ ተጠይቀው ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።   

የምጣኔ ሃብት ተጠባቢዎችና ሌበር ፓርቲ ፖሊሲው የወጣቶችን ቀልብ ለመሳብ የታቀደ የመጨረሻ ደቂቃ ሙከራ እንጂ የቤት ችግርን የሚፈታ አይደለም። ከቶውንም ተቀማጭ የጡረታ አበላቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳደር ነው በሚል ትችቶችን ሰንዝረዋል።  

የግሪንስ የምርጫ ዘመቻ                                                     

የአውስትራሊያ ግሪንስ ፓርቲ ዛሬ ሰኞ ምሽት የ173 ቢሊየን ዶላርስ ይፋ የምርጫ ዘመቻውን ይከፍታል። 

የግሪንስ ፓርቲ ቅዳሜ ሜይ 21 / ግንቦት 13 በሚካሔደው አገራዊ ምርጫ የስልጣን ሚዛንን መጨበጥ ከቻለ ሰባት ቁልፍ ፖሊሲዎቹን ይዞ ከሌበር ፓርቲ ጋር ለመደራደር ውጥን መያዙን የፓርቲው መሪ አዳም ባንድት አስታውቀዋል።  

በግሪንስ የመደራደሪያ ዝርዝር ውስጥ የጥርስና የአዕምሮ ጤና ሜዲኬይር ውስጥ እንዲታከል፣ አዲስ የጋዝና የደንጊያ ከሰል ማምረቻዎች እንዳይገነቡ፣ ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ቤቶች እንዲገነቡ፣ ነፃ የሙዋዕለ ሕፃናት አገልግሎት፣ የተማሪዎች ዕዳ ስረዛ፣ የገቢ ድጎማ ጭማሪና የኡሉሩ መግለጫን ግብር ላይ ማዋል የሚሉ ሠፈረውበታል። 

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now