ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አወዛጋቢው የመኖሪያ ቤት ፖሊሲያቸው የቤቶች ዋጋ ንረትን አያስከትለም ብለው እየተከራከሩ ነው

***የአውስትራሊያ ግሪንስ ፓርቲ ዛሬ ሰኞ ምሽት የ173 ቢሊየን ዶላርስ ትልም ይፋ የምርጫ ዘመቻውን ይከፍታል።

News

Aerial view of construction work and housing in Western Sydney on November 13, 2017 in Sydney, Australia. Source: Getty

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የመጀመሪያ ጊዜ ቤት ገዢዎች ከጡረታ አበል ተቀማጫቸው ላይ 40 ፐርሰንት - እስከ $50,000 ወጪ ማድረግ እንዲችሉ የሚፈቅደው  የፓርቲያቸው የመኖሪያ ቤት ፖሊሲ የቤት ዋጋ ንረትን አያስከትልም ሲሉ እየተከራከሩ ነው።  

የጡረታ አበል ሚኒስትር ጄን ሂዩም ግና ዛሬ ጠዋት በሰጡት መግለጫ ፖሊሲው የአጭር ጊዜ የቤቶች ዋጋ ንረትን ሊያስከትል እንደሚችል አምነዋል።

ይሁንና አቶ ሞሪሰን በዕድሜ የገፉ አውስትራሊያውያን ትላልቅ ቤቶቻቸውን ሸጠው ከሽያጩ እስከ $300,000 ወደ ጡረታ አበላቸው እንዲጨምሩ የሚፈቅደው ፖሊሲ የቤቶች የዋጋ ንረት እንዳያሻቅብ ይረዳል ሲሉ ተከራክረዋል። 

አቶ ሞሪሰን የመኖሪያ ቤት ፖሊሲያቸው የገበያ ሁኔታ አመላካች ሞዴል ተሠርቶለት እንደሁና ሞዴሉንም ይፋ ያደርጉ እንደሁ ተጠይቀው ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።   

የምጣኔ ሃብት ተጠባቢዎችና ሌበር ፓርቲ ፖሊሲው የወጣቶችን ቀልብ ለመሳብ የታቀደ የመጨረሻ ደቂቃ ሙከራ እንጂ የቤት ችግርን የሚፈታ አይደለም። ከቶውንም ተቀማጭ የጡረታ አበላቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳደር ነው በሚል ትችቶችን ሰንዝረዋል።  

የግሪንስ የምርጫ ዘመቻ                                                     

የአውስትራሊያ ግሪንስ ፓርቲ ዛሬ ሰኞ ምሽት የ173 ቢሊየን ዶላርስ ይፋ የምርጫ ዘመቻውን ይከፍታል። 

የግሪንስ ፓርቲ ቅዳሜ ሜይ 21 / ግንቦት 13 በሚካሔደው አገራዊ ምርጫ የስልጣን ሚዛንን መጨበጥ ከቻለ ሰባት ቁልፍ ፖሊሲዎቹን ይዞ ከሌበር ፓርቲ ጋር ለመደራደር ውጥን መያዙን የፓርቲው መሪ አዳም ባንድት አስታውቀዋል።  

በግሪንስ የመደራደሪያ ዝርዝር ውስጥ የጥርስና የአዕምሮ ጤና ሜዲኬይር ውስጥ እንዲታከል፣ አዲስ የጋዝና የደንጊያ ከሰል ማምረቻዎች እንዳይገነቡ፣ ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ቤቶች እንዲገነቡ፣ ነፃ የሙዋዕለ ሕፃናት አገልግሎት፣ የተማሪዎች ዕዳ ስረዛ፣ የገቢ ድጎማ ጭማሪና የኡሉሩ መግለጫን ግብር ላይ ማዋል የሚሉ ሠፈረውበታል። 

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service