በአፍሪካ በፀጥታ ችግሮች ምክንያት ስኬቶች ወደ ኋላ እንዳይመለሱ የጋራ ትብብር እንደሚያስፈልግ ጉተሬዝ አሳሰቡ

የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ “የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ሐሳብ ቅዳሜና እሁድ የካቲት 11 እና 12 በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

UN Secretary General Antonio Guterres.jpg

UN Secretary-General Antonio Guterres. Credit: SIMON MAINA/AFP via Getty Images

ለአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ የተገኙት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሐማት ውይይት አድርገዋል።

የሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ እና የተመዱ ዋና ፀሐፊ ጉተሬዝ በዋናነት በአፍሪካ የሰላም እና የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ነው የተወያዩት።

ሙሳ ፋኪ ከውይይቱ በኋላ በማኅበራዊ በትዊተራቸው እንደገለፁት "በአፍሪካ በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ድሎች በፀጥታ ችግሮች ምክንያት ወደ ኋላ የመመለስ ስጋት እንዳይኖርባቸው በጋራ ሊሠሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል" ብለዋል።

የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ “የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ሐሳብ ቅዳሜና እሁድ የካቲት 11 እና 12 በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በአሁኑ ወቅት በጉባኤው ለመሳተፍ የሀገራት መሪዎች አዲስ አበባ እየገቡ ነው።

በዛሬው ዕለትም የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ፣ የሌሴቶ ፕሬዚዳንት ሳም ማትኬኔ፣ የኬፕ ቬርዴ ፕሬዚዳንት ሆዜ ማሪያ ፔሬራ፣ የሞሪታኒያው ፕሬዚዳንት መሐመድ ኦውልድ ጋውዛኒ እና ሌሎችም መሪዎች አዲስ አበባ ገብተዋል።

[ደመቀ ከበደ ፡ ከአፍሪካ ሕብረት ፡ አዲስ አበባ]

Share

Published

Updated

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service