Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

በአፍሪካ በፀጥታ ችግሮች ምክንያት ስኬቶች ወደ ኋላ እንዳይመለሱ የጋራ ትብብር እንደሚያስፈልግ ጉተሬዝ አሳሰቡ

የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ “የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ሐሳብ ቅዳሜና እሁድ የካቲት 11 እና 12 በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

UN Secretary General Antonio Guterres.jpg

UN Secretary-General Antonio Guterres. Credit: SIMON MAINA/AFP via Getty Images

ለአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ የተገኙት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሐማት ውይይት አድርገዋል።

የሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ እና የተመዱ ዋና ፀሐፊ ጉተሬዝ በዋናነት በአፍሪካ የሰላም እና የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ነው የተወያዩት።

ሙሳ ፋኪ ከውይይቱ በኋላ በማኅበራዊ በትዊተራቸው እንደገለፁት "በአፍሪካ በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ድሎች በፀጥታ ችግሮች ምክንያት ወደ ኋላ የመመለስ ስጋት እንዳይኖርባቸው በጋራ ሊሠሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል" ብለዋል።

የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ “የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ሐሳብ ቅዳሜና እሁድ የካቲት 11 እና 12 በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በአሁኑ ወቅት በጉባኤው ለመሳተፍ የሀገራት መሪዎች አዲስ አበባ እየገቡ ነው።

በዛሬው ዕለትም የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ፣ የሌሴቶ ፕሬዚዳንት ሳም ማትኬኔ፣ የኬፕ ቬርዴ ፕሬዚዳንት ሆዜ ማሪያ ፔሬራ፣ የሞሪታኒያው ፕሬዚዳንት መሐመድ ኦውልድ ጋውዛኒ እና ሌሎችም መሪዎች አዲስ አበባ ገብተዋል።

[ደመቀ ከበደ ፡ ከአፍሪካ ሕብረት ፡ አዲስ አበባ]


1 min read

Published

Updated

By Demeke Kebede

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now