ቴዎድሮስ ምህረት ከበደ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ሆነው ተሾሙ

አቶ ቴዎድሮስ ምህረትና ወ/ሮ አበባ እምቢያለ በፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚደንት የተሾሙት፤ የቀድሞዋ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊና የቀድሞው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 9 በፈቃዳቸው የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ለምክር ቤቱ ማስገባታቸውን ተከትሎ ነው።

Tewodros Mihret Kebede.jpg

Tewodros Mihret Kebede, President of the Federal Supreme Court of Ethiopia. Credit: PR

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡

ምክር ቤቱ በስብሰባው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረቡ ሹመቶችን መርምሮ እያፀደቀ ነው፡፡

በዚህም አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ከበደ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው ሲሾሙ ወ/ሮ አበባ እምቢያለ መንግሥቴ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾመዋል፡፡

ተሿሚዎች በጉባኤው ፊት ቀርበው ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል።

አቶ ቴዎድሮስ ምህረትና ወ/ሮ አበባ እምቢያለ በፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚደንት የተሾሙት፤ የቀድሞዋ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊና የቀድሞው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 9 በፈቃዳቸው የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ለምክር ቤቱ ማስገባታቸውን ተከትሎ ነው።
Meaza Ashenafi.jpg
Meaza Ashenafi, former President of the federal Supreme Court of Ethiopia. Credit: ullstein bild via Getty Images
አቶ ቴዎድሮስ አዲሱን የሥራ ኃላፊነታቸውን ከመቀበላቸው በፊት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሕግ ትምህርት ቤት መምህርና ነገረ ፈጅ ነበሩ። የኢትዮጵያ የሕግ ባለ ሙያዎች ማኅበርንም በፕሬዚደንትነት አገልግለዋል።

በምክትል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንትነት ቃለ መሐላ የፈፀሙት ወ/ሮ አበባ እምቢያለ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ፣ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትና በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት ሠርተዋል።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service