የዓለም ዋንጫ ሊጠናቀቅ አንድ ንጋት ሲቀረው ለሶስተኛ ደረጃ ፍልሚያ በበቁት ቡድናት መካከል በተካሔደው ግጥሚያ ክሮኤሽያ ሞሮኮን በዓል- ራይን ስታዲየም 2 ለ 1 ረትቷል።
ግቦቹን ለክሮኤሽያ ያስቆጠሩት ጆሽኮ ቫርዲዮል ጨዋታው በተጀመረ በ7ኛው ደቂቃ ሲሆን፤ አሽራፍ ዳሪ አስከትሎ በ9ኛው ደቂቃ ለሞሮኮ አቻ ግብ አስቆጥሯል።
ይሁንና ሚስላቭ ኦርቺች በ42ኛው ደቂቃ ለክሮኤሽያ ሁለተኛዋን ግብ ከመረብ ለማዋደደ በመብቃቱና ከሞሮኮ በኩል ለአቻነት የሚያበቃ ግብ ባለመቆጠሩ የግጥሚያው ፍፃሜ ሆኗል።

የዓለም ዋንጫ 63ኛው ግጥሚያምም በዚሁ አብቅቷል።
ቀሪው 64ኛውና የመጨረሻው ግጥሚያና የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ዛሬ እኩለ ለሊት ይጀምራል።
የፍፃሜ ግጥሚያ ሠንጠረዥ
ፈረንሳይ እና አርጀንቲና (ሰኞ ዲሴምበር 19 / ታሕሳስ 9) 2:00 am [AEDT]

