የአውስትራሊያ ሥራ አጦች ቁጥር ወደ 3.7 ከፍ አለ

ቻይና የአውስትራሊያ ጣውላ ላይ ጥላ የነበረውን ማዕቀብ በማንሳት ከዛሬ ጀምሮ ወደ አገሯ እንዲገባ ፈቀደች

SBS Amharic News Podcast World.jfif

Credit: SBS Amharic

የአውስትራሊያ ሥራ አጦች ቁጥር ካለፈው ወር በ 0.8 ፐርሰንት ከፍ በማለት 3.7 ፐርሰንት ደርሷል።

ለሥራ አጦች ቁጥር መጨመር አስባብ የሆነው 4,300 ሰዎች ሥራቸውን በማጣታቸውና የሠራተኞች ተሳትፎ በ 0.1 ፐርሰንት ዝቅ በማለቱ እንደሆነ የአውስትራሊያ ስታቲስቲክ ቢሮ አመልክቷል።

የፌዴራል በጅሮንድ ጂም ቻልመርስ፤ መንግሥት የሥራ አጥ ቁጥር እንደሚጨምር ይጠብቅ እንደነበረና ሆኖም ከዓለም አቀፍ የሥራ አጦች ቁጥር ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ይሁንና የተቃዋሚ ቡድን ምክትል መሪ ሱዛን ሊ ግና የሥራ አጥ ቁጥሩ በ 0.8 ፐርሰንት መጨመር "አሳሳቢ" ነው ብለውታል።
 
ቻይና - አውስትራሊያ

ቻይና ከዛሬ ጀምሮ የአውስትራሊያ ጣውላ ወደ አገሯ መግባቱን እንዲቀጥል መፍቀዷን አስታወቀች።

ቻይና ጣውላን ጨምሮ በሌሎችም የአውስትራሊያ የውጭ አቅርቦት ምርቶች ላይ ከ2020 አንስቶ ምጣኔ ሃብታዊ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።

ውሳኔው የአውስትራሊያን የንግድ ሚኒስትር ዶን ፋረልን ባለፈው ሳምንት የቤጂንግ ጉብኝት ተከትሎ መካሄዱ የሁለቱ አገራት ዲፖሎማሲያዊ ግ ንኙነቶች የመሻሻል ፍንጭ እንደሆነ ተተርጉሟል።
 
በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር ሺያዖ ቺያን፤ የአገራቸው ጉምሩክ ባለስልጣናት የአውስትራሊያ ጣውላ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ቻይና እንዲዘልቅ መፈቀዱን ለአውስትራሊያ ግብርና ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ዛሬ ሐሙስ ሜይ 18 በኤምባሲያቸው ቅጥር ግቢ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ ተናግረዋል።


 


Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service