SKIP TO MAIN CONTENT

የአውስትራሊያ ሥራ አጦች ቁጥር ወደ 3.7 ከፍ አለ

ቻይና የአውስትራሊያ ጣውላ ላይ ጥላ የነበረውን ማዕቀብ በማንሳት ከዛሬ ጀምሮ ወደ አገሯ እንዲገባ ፈቀደች

SBS Amharic News Podcast World.jfif
Credit: SBS Amharic

1 min read

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Skip to article content

የአውስትራሊያ ሥራ አጦች ቁጥር ካለፈው ወር በ 0.8 ፐርሰንት ከፍ በማለት 3.7 ፐርሰንት ደርሷል።

ለሥራ አጦች ቁጥር መጨመር አስባብ የሆነው 4,300 ሰዎች ሥራቸውን በማጣታቸውና የሠራተኞች ተሳትፎ በ 0.1 ፐርሰንት ዝቅ በማለቱ እንደሆነ የአውስትራሊያ ስታቲስቲክ ቢሮ አመልክቷል።

የፌዴራል በጅሮንድ ጂም ቻልመርስ፤ መንግሥት የሥራ አጥ ቁጥር እንደሚጨምር ይጠብቅ እንደነበረና ሆኖም ከዓለም አቀፍ የሥራ አጦች ቁጥር ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ይሁንና የተቃዋሚ ቡድን ምክትል መሪ ሱዛን ሊ ግና የሥራ አጥ ቁጥሩ በ 0.8 ፐርሰንት መጨመር "አሳሳቢ" ነው ብለውታል።

 

ቻይና - አውስትራሊያ

ቻይና ከዛሬ ጀምሮ የአውስትራሊያ ጣውላ ወደ አገሯ መግባቱን እንዲቀጥል መፍቀዷን አስታወቀች።

ቻይና ጣውላን ጨምሮ በሌሎችም የአውስትራሊያ የውጭ አቅርቦት ምርቶች ላይ ከ2020 አንስቶ ምጣኔ ሃብታዊ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።

ውሳኔው የአውስትራሊያን የንግድ ሚኒስትር ዶን ፋረልን ባለፈው ሳምንት የቤጂንግ ጉብኝት ተከትሎ መካሄዱ የሁለቱ አገራት ዲፖሎማሲያዊ ግ ንኙነቶች የመሻሻል ፍንጭ እንደሆነ ተተርጉሟል።

 

በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር ሺያዖ ቺያን፤ የአገራቸው ጉምሩክ ባለስልጣናት የአውስትራሊያ ጣውላ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ቻይና እንዲዘልቅ መፈቀዱን ለአውስትራሊያ ግብርና ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ዛሬ ሐሙስ ሜይ 18 በኤምባሲያቸው ቅጥር ግቢ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ ተናግረዋል።

 


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now