አውስትራሊያ ለምዕራብ ኢየሩሳሌም የእሥራኤል መዲናነት ሰጥታ የነበረውን ዕውቅና ሻረች

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ፤ አውስትራሊያ ሁሌም ሁነኛ የእሥራኤል ወዳጅ እንደሆነችና ለፍልስጥኤም ሕዝብም ረድኤትን ጨምሮ የማይናወጥ ድጋፍ እንዳላት አመላክተዋል።

Australian Foreign Minister Penny Wong.jpg

Australian Foreign Minister Penny Wong. Credit: Lukas Coch - Pool/Getty Images

የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ አውስትራሊያ ቀደም ሲል ለምዕራብ ኢየሩሳሌም በእሥራኤል መዲናነት ሰጥታ የነበረውን ዕውቅና መሻሯን አስታወቁ።

 ሚኒስትሯ ኢየሩሳሌም ዋና ከተማነት ዕውቅና የሰላም ድርድሩ ከፍልስጥኤም ሕዝብ ጋር ዕልባት እስኪያገኝ ድረስ ይሁንታን አንደማያገኝ ገልጠዋል።

የቀድሞው የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚንኒስትር ስኮት ሞሪሰን የፕሬዚደንት ትራምፕን የ2017 የዩናይትድ ኤምባሲን ከቴል አቪቭ ወደ ምዕራብ ኢየሩሳሌም የማዞር ውሳኔ ተከትለው በዲሴምበር 2018 አውስትራሊያ ምዕራብ ኢየሩሳሌምን በእሥራኤል መዲናነት ዕውቅና እንድትቸር አድርገው ነበር።  

ሴናተር ዎንግ በ2018 ሌበር ተቃዋሚ በነበረት ወቅት የኢየሩሳሌም ዋና ከተማነት በኢሥራኤልና ፍልስጥኤም መካከል በሰላማዊ ድርድር ዕልባት እስኪያገኝ ድረስ ለኢየሩሳሌም የመዲናነት ዕውቅና መስጠትን ተቃውሞ እንደነበርና አሁን በመንግሥትነት ውሳኔውን እንደሻረ አስታውቀዋል።

አቶ ሞሪሰንም ከአብዛኛው ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የተስፈነጠሩ እንደነበር ተናግረዋል።

አክለውም፤ መንግሥታቸው ለሁለት መንግሥታት መፍትሔ ኃላፊነት የተመላበት ድጋፉን በመቸር እንደሚቀጥልና የአውስትራሊያ ኤምባሲም ቴል አቪቭ ውስጥ እንደሚቆይ ገልጠዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዎንግ፤ አውስትራሊያ ሁሌም ሁነኛ የእሥራኤል ወዳጅ እንደሆነችና ለፍልስጥኤም ሕዝብም ረድኤትን ጨምሮ የማይናወጥ ድጋፍ እንዳላት አመላክተዋል።



 



 


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service