የኢትዮጵያ መንግሥት በአንድ በኩል ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነትን እያስጠበቅኩ በሌላ በኩል ለአፍሪካ ኅብረት የሰላም ውይይት ዝግጁ ነኝ አለ

የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተሞች ውስጥ እንዳይካሔድ ጥንቃቄ እያደረገ እንደሚገኝም ገለጠ

A flag with a peace dove covers the sun.jpg

A flag with a peace dove covers the sun. Credit: Frank Hammerschmidt/picture alliance via Getty Images

የኢትዮጵያ መንግሥት ጥቅምት 7 ቀን 2015 የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር የአስቸኳይ ተኩስ አቁምና የሰብዓዊ ረድዔት ይቀጥል ጥሪን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በኅብረቱ አማካኝነት ለሚካሔደው የሰላም ውይይት ዝግጁ ስለመሆኑ ገልጧል።

አያይዞም፤ መንግሥት የአገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን፣ የፌዴራል ተቋማትን፣ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችንና በተለይም የአየር ክልልን የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ጠቁሟል።

አክሎም፤ እኒህን ዓላማዎቹን በአንድ በኩል እያስፈፀመ፤ በሌላ በኩል በአፍሪካ ኅብረት በኩል ለሚካሔደው የሰላም ውይይት ዝግጁነቱን አመላክቷል።


ሕዝብና ሠራተኞችም ከሕወሓት ወታደራዊ ተቋማት እንዲርቁ ሲልም አሳስቧል።

በማጠቃለያውም "በትግራይ ክልል የሚገኙ ዜጎቹን ደኅንነት ለመጠበቅ በሕግ የተሰጠውን ሕገ መንግሥታዊ ግዴታውን ለመወጣት የኢትዮጵያ መንግሥት ያለውን ዝግጁነት በዚህ አጋጣሚ ያረጋግጣል" ብሏል።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service