የኢትዮጵያ መንግሥት በአንድ በኩል ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነትን እያስጠበቅኩ በሌላ በኩል ለአፍሪካ ኅብረት የሰላም ውይይት ዝግጁ ነኝ አለ

የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተሞች ውስጥ እንዳይካሔድ ጥንቃቄ እያደረገ እንደሚገኝም ገለጠ

A flag with a peace dove covers the sun.jpg

A flag with a peace dove covers the sun. Credit: Frank Hammerschmidt/picture alliance via Getty Images

የኢትዮጵያ መንግሥት ጥቅምት 7 ቀን 2015 የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር የአስቸኳይ ተኩስ አቁምና የሰብዓዊ ረድዔት ይቀጥል ጥሪን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በኅብረቱ አማካኝነት ለሚካሔደው የሰላም ውይይት ዝግጁ ስለመሆኑ ገልጧል።

አያይዞም፤ መንግሥት የአገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን፣ የፌዴራል ተቋማትን፣ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችንና በተለይም የአየር ክልልን የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ጠቁሟል።

አክሎም፤ እኒህን ዓላማዎቹን በአንድ በኩል እያስፈፀመ፤ በሌላ በኩል በአፍሪካ ኅብረት በኩል ለሚካሔደው የሰላም ውይይት ዝግጁነቱን አመላክቷል።

ሕዝብና ሠራተኞችም ከሕወሓት ወታደራዊ ተቋማት እንዲርቁ ሲልም አሳስቧል።

በማጠቃለያውም "በትግራይ ክልል የሚገኙ ዜጎቹን ደኅንነት ለመጠበቅ በሕግ የተሰጠውን ሕገ መንግሥታዊ ግዴታውን ለመወጣት የኢትዮጵያ መንግሥት ያለውን ዝግጁነት በዚህ አጋጣሚ ያረጋግጣል" ብሏል።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now