በርዕደ መሬት ሳቢያ በሶሪያና ተርኪዬ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ከ46 ሺህ አለፈ

የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ሕዝበ ውሳኔ በዚህ ዓመት በወርኅ ኦክቶበር ወይም ዲሴምበር ውስጥ ሊከናወን እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ጠቆሙ።

Turkiye.jpg

Members of the Turkish IHH Search and Rescue Team searched a site of collapsed buildings after a powerful earthquake, in Hatay, Türkiye. Credit: MARTIN DIVISEK/EPA

በሶሪያና ተርኪዬ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ46 ሺ ያለፈ ሲሆን፤ ከቶውንም የሟቾች ቁጥር ሊንር እንደሚችል ይጠበቃል።

አያሌ ሰዎች እስካሁንም የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን፤ ከፍርስራሾች ስር ሆነው የድረሱልን ጥሪ የሚያሰሙ ድምፆችንም የድንገተኛ አደጋ ደራሽ ሠራተኞች እየሰሙ መሆኑ ተነግሯል።

ተርኪዬ ውስጥ በደረሰው አደጋ 264 ሺህ ያህል አፓርትመንቶች ወድመዋል።

 ሶሪያ ውስጥ የአደጋው ሰለባ የሆኑ ሰዎች ጉዳይ አሳስቢ የሆነ መሆኑን የዓለም ምግብ ፕሮግራም ያመለከተ ሲሆን፤ በሰሜናዊ ምዕራብ በኩል በመቶ ሺህዎች ለሚቆጠሩ እርዳታ ፈላጊዎች እገዛዎችን ለማድረስ እንዲችል የሶሪያ ባለስልጣናትን እየወተወተ መሆኑን ገልጧል።

 ድምፅ ለፓርላማ

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ለነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ሕዝበ ውሳኔ በወርኅ ኦክቶበር ወይም ዲሴምበር ሊካሔድ እንደሚችል ጠቆሙ።

አቶ አልባኒዚ ሕዝበ ውሳኔው ከፌዴሬሽን ምሥረታ 100 ዓመታት ወዲህ ይህ ወሳኝ መልካም ዕድል እንደሆነ አስገንዝበው፤ መሪዎች ዕድሉን በቀናነት ተመልክተው ድጋፋቸውን እንዲቸሩት ጥሪ አቅርበዋል።

ድምፅ ለፓርላማ ነባር ዜጎች በሆኑና ባልሆኑ ዜጎች መካከል ያሉትን ልዩነቶችን ማጥበቢያ፣ ዕርቅና ምክክር እንደሆነም አመላክተዋል።




Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service