"ፀፀቶች የሉኝም"የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር የሥራ ኃላፊነታቸውን እንደሚለቁና ከፖለቲካውም ዓለም እንደሚሰናበቱ አስታወቁ

"መታወስ የምሻው ሁሌም መልካም ለመሆን እንደሚጥር ሰው ነው" የኒውዝላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አደርን

PM acinda Ardern .jpg

Prime Minister Jacinda Ardern announces her resignation at the War Memorial Centre on January 19, 2023 in Napier, New Zealand. Credit: Getty / AFP

የ37 ዓመቷ የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደን ከጠቅላይ ሚኒስትራዊ የሥራ ኃላፊነትቸውና ከፖለቲካው ዓለም እንደሚሰናበቱ ዛሬ ሐሙስ ጃኑዋሪ 19 / ጥር 11 አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ከሥራቸው ለመሰናበት የወሰኑት ለሚቀጥለው ምርጫ ለውድደር ለመቅረብና በቀጣይነትም ለመዝለቅ ውስጣቸው የቀረ ኃይል የሌለ በመሆኑና እንዲያ ባለ ሁኔታ መቀጠሉ "አገሪቱን መበደል" እንደሚሆን በመገንዘብ መሆኑን ገልጠዋል።

በታካይነትም ቀሪ ጊዜያቸውን ከቤተሰባቸው ጋር ለማሳለፍ መሻታቸውም ሌላኛው አስባብ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንኑ የማይቀለብሱትን ከሥልጣን የመልቀቅ ውሳኔያቸውን ዛሬ ጠዋት ለካቢኔያቸው ሲያሳውቁ አባላቱ በውሳኔያቸው ግር መሰኘታቸውንና የተወሰኑ የቤተሰባቸው አባላት በሥራቸው እንዲቀጥሉ ያበረታቷቸው መሆኑን ገልጠዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው የአገልግሎት ጊዜያት የወጠኑትን ግብር ላይ በማዋላቸው "ፀፀቶች የሉኝም፤ የተቻለኝን ያህል መከወኔን አውቃለሁና" ብለዋል።

እንደምን ሊታሰቡ እንደሚሹ ከጋዜጠኞች ተጠይቀው ሲመልሱ "መታወስ የምሻው ሁሌም መልካም ለመሆን እንደሚጥር ሰው ነው" ሲሉ መልሰዋል።

ለቤተሰባቸው ያላቸውን መልዕክት ሲያስተላልፉም፤

በቀዳሚነት ለአራት ዓመት ሴት ልጃቸው ኔቭ "ኔቭ፤ በዚህ ዓመት ትምህርት ቤት ስትጀምሪ እናትሽ እዚያ ለመገኘት ትሻለች"

ለፍቅረኛቸው "ክላርክ፤ ጋብቻችንን እንፈፅም" ብለዋል።

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በቲዊተር ገፃቸው ለኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ያላቸውን የአመራር ክህሎት አድናቆትና ወዳጅነታቸውን አንስተው አመላክተዋል።
ከአያሌ አድናቂዎቻቸውም በርካታ የአድናቆትና መልካም ምኞት መልዕክቶች እየጎረፉላቸው ነው።

Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service