Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ኪየቭ ውስጥ የዩክሬይን የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትርን ጨምሮ ከደርዘን በላይ ሰዎች በሂሊኮፕተር አደጋ ሕይወታቸው አለፈ

በሂሊኮፕተር አደጋው የዩክሬይን አንደኛ ተቀዳሚ የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትር የቭሄኒይ የኒን እና የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ፀሐፊ ሕይወትም አልፏል።

Ukrainian Interior Minister Denys Monastyrsky .jpg

KYIV, UKRAINE - 2022/05/05: Ukrainian Interior Minister Denys Monastyrsky is seen during a visit at the Hostomel Airfield, after the battles with Russian troops. Russia invaded Ukraine on 24 February 2022, triggering the largest military attack in Europe since World War II. Credit: Pavlo Gonchar/SOPA Images/LightRocket via Getty Images

ከዩክሬይን የአገርው ውስጥ ሚኒስትር ጋር አንድ ሕፃንን ጨምሮ የ14 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን፤ የፈረንሳይ ሥሪት የሆነችው ሱፐር ፑማ ሄሊኮፕተር በመዲናይቱ ኪየቭ ክፍለ ከተማ ውስጥ ከሚገኝ አንድ አፀደ ሕፃናት ቅጥር ግቢ ላይ ተከስክሳለች።

በአደጋው በ2021 በፕሬዚደንት ቮሎድሚይር ዘለንስኪ የተሾሙት የአገር ውስጥ ሚኒስትር ዴኒስ ሞናህስቲርስኪ ሕይወት ማለፉን የዩክሬይን ብሔራዊ ፖሊስ ዋን አዛዥ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

በሂሊኮፕተር አደጋው የዩክሬይን አንደኛ ተቀዳሚ የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትር የቭሄኒይ የኒን እና የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ፀሐፊ ሕይወትም አልፏል።

Fragments of the helicopter lie on the playground at the site of a helicopter crash .jpg
Fragments of the helicopter lie on the playground at the site of a helicopter crash on January 18, 2023 in Brovary, Ukraine. Credit: Oleksii Samsonov /Global Images Ukraine via Getty Images

ከሂሊኮፕተር አደጋው ጋር ተያይዞ የአንድ ልጅ ሕይወት ሲያልፍ ሶስት በብርቱ ቆስለዋል።

ፕሬዚደንት ዜሌንስኪ በአደጋው ሳቢያ ሕይወታቸውን ላጡት ዩክሬናውያን የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን የገለጡ ሲሆን፤ በተለይም የግልና የቤተሰባቸው በእጅጉ የቅርብ ጓደኛ የነበሩት የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትሩ ዴኒስ ሞናህስቲርስኪ ሞት በእጅጉ ዘልቆ የተሰማቸውና ጎጂ መሆኑን ተናግረዋል።

 


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now