በአውስትራሊያና ኒውዝላንድ አስተናጋጅነት ሐምሌ 14 ተጀምሮ ዛሬ ነሐሴ 14 የተጠናቀቀው የ2023 የፊፋ የሴቶች ዓለም ዋንጫ በስፔይን አሸናፊነት በሲድኒ አውስትራሊያ ስታዲየም ተጠናቅቋል።
ስፔይን እንግሊዝን 1 ለ 0 አሸንፋ ለዓለም ሻምፒዮናነት ያበቃቻን ግብ በ29ኛው ደቂቃ መረብ ላይ ያሳረፈችው ኦልጋ ካርሞና ናት።
ከ1991 አንስቶ እስከ 2023 ለዘጠኝ ጊዜያት በተካሔደው የሴቶች እግር ኳስ የዓለም ዋንጫ ዩናይትድ ስቴትስ ለአራት ጊዜያት (1991፣ 1999፣ 2015፣ 2019)፣ ጀርመን (2003፣ 2007) ኖርዌይ (2015) ጃፓን (2011) እና ስፔይን (2023) ለሻምፒዮናነት በቅተዋል።
በዕለቱ በተካደው የሽልማት ሥነ ሥርዓት የ19 ዓመቷ የስፔይን ተጫዋቿ ሳልማ ፐሬሉዌሎ የምርጥ ወጣት ተጫዋች ዋንጫ ወስዳለች።

በፍፃሜው ጨዋታ ወቅት የስፔይንን ፍፁም ቅጣት ምት ከግብነት ያዳነችው የእንግሊዟ ግብ ጠባቂ ሜሪ ኢርፕስ የወርቅ እጅ ጓንት ሽልማት ተሸልማለች።

ኤይታና ቦንማቲ የፍፃሜ ጨዋታው ምርጥ ተጫዋች ሆና የወርቅ ኳስ ለመሸለም በቅታልች ።

ድል አድራጊዋ ስፔይን የወርቅ ሜዳልና የ2023 የፊፋ ዓለም ዋንጫ በእጇ አስገብታለች።

ለሻምፒዮናነት ታስባ ሁለተኛ የወጣችው እንግሊዝ የብር ሜዳል ተቀብላለች።

የፊፋ ሴቶች የዓለም ዋንጫ እንደ ወንዶቹ በየአራት ዓመቱ የሚካሔድ ሲሆን፤ ቀጣዩ የ2027 ዓለም ዋንጫ የሚካሔደው ደቡብ አፍሪካ ነው።

