የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር በ59ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤው ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለሰጡ ሁለት ሐኪሞች የህይወት ዘመን ሽልማትን አበረከተ።
ዶክተር ይርጉ ገብረህይወት በወንድ ጾታ እንዲሁም ዶክተር ተቋም ደበበ ደግሞ በሴት የህይወት ዘመን ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ተሸላሚዎቹ በ ሙያቸው የተሻለ የሕክምና አገልግሎት እንደሰጡ በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
ማህበሩ ከህይወት ዘመን ሽልማት በተጨማሪ ዶክተር ትህትና ንጉሴን በሴት ወጣት ተጽዕኖ ፈጣሪ ሐኪም በሚል ሲሸልም ዶክተር ፈቀደ አግዋርን ደግሞ በወንድ ወጣት ተጽዕኖ ፈጣሪ ሐኪም በማለት ሸልሟል።
አዲስ ህይወት የማገገሚያ ማዕከል ደግሞ የዓመቱ ምርጥ የጤና ተቋም በሚል ዕውቅና ተሰጥቶታል።
ሽልማቱን የጤና ሚንስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ተግባር ይግዛው ሰጥተዋል።