በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል በቀጣዩ ሳምንት የሰላም ንግግር ሊደረግ ነው

የሰላም ንግግሩ ይካሔዳል ተብሎ የታሰበው ደቡብ አፍሪካ ነው።

Ambassador Redwan Hussien.jpg

Ambassador Redwan Hussien, National Security Advisor to Prime Minister Abiy Ahmed. Credit: Erhan Elaldı/Anadolu Agency via Getty Images

በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እማካይነት በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል የሰላም ንግግር ለማካሔድ ኦክቶበር 24 ቀን 2022 ደቡብ አፍሪካ እንዲካሔድ ቀን መቆረጡ ተገለጠ።

የሰላም ንግግሩን ለማካሔድ ቀን ቆርጦ ግብዣ ያቀረበው የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን መሆኑን ያስታወቁት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የፀጥታ አማካሪ ናቸው።

የሰላም ንግግሩ ዕሳቤ አዲስ ሳይሆን ቀደም ሲልም ኦክቶበር 8 በተመሳሳይ መልኩ ደቡብ አፍሪካ እንደሚካሔድ በአፍሪካ ኅብረት በኩል ለሁለቱ ወገኖች ጥሪ ቀርቦ ያለስኬት መክኖ ቀርቷል።

በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና በሕወሓት ጦር መካከል የሚደረገው ወታደራዊ ግጭት አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል።

በዚህ ሳምንት ውስጥ ከመንግሥት በተሰጠ መግለጫ ሽሬ፣ አላማጣና ቆቦ ከተሞችን ከሕወሓት እጅ አውጥቶ በቁጥጥሩ ስር ማድረጉን ገልጧል።

አምባሳደር ሬድዋን መንግሥታቸው በሰላም ንግግሩ ላይ ተሳታፊ እንደሚሆን ቢያስታውቁም በሕወሓት በኩል እስካሁን የተሳታፊት ማረጋገጫም ሆነ የእምቢታ ቃሎች ገና አልተደመጡም።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service