ሊዝ ትረስ ከእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው በ44ኛ ቀናቸው ለቀቁ

ሊዝ ትረስ በሚቀጥለው ሳምንት አዲስ ተኪ እስኪያገኙ ድረስ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ይቆያሉ

Prime Minister Liz Truss announces her resignation at Downing Street.jpg

Prime Minister Liz Truss announces her resignation at Downing Street on October 20, 2022 in London, England. Credit: Rob Pinney/Getty Images

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ ከ44 ቀናት በኋላ ስልጣናቨውን ለመልቀቅ ግድ ተሰኝተዋል። ይህም በእንግሊዝ ታሪክ ለአጭር ጊዜ በመሪነት የቆዩ መሪ አድርጓቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ከስልጣን እንደሚለቁ ለንጉሥ ቻርልስ ማስታወቃቸውን አካትተው ሁለት ደቂቃ ያልሞላ ንግግር አድርገው ከጋዜጠኞች ጥያቄ ሳይቀበሉ ወደ ቢሮአቸው ተመልሰዋል።

ተኪያቸውም በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በወግ አጥባቂው ፓርቲ እንደሚመረጥ ይጠበቃል።

ዛሬና ነገ ከወግ አጥባቂው ፓርቲ የምክር ቤት አባላት ውስጥ ሊዝ ትረስን ለመተካት ዕጩዎች ይቀርባሉ።

ይህም እንግሊዝ በአራት ወራት ውስጥ ሶስተኛ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሰየም ግድ ትሰኛለች።




Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service