ሊዝ ትረስ ከእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው በ44ኛ ቀናቸው ለቀቁ

ሊዝ ትረስ በሚቀጥለው ሳምንት አዲስ ተኪ እስኪያገኙ ድረስ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ይቆያሉ

Prime Minister Liz Truss announces her resignation at Downing Street.jpg

Prime Minister Liz Truss announces her resignation at Downing Street on October 20, 2022 in London, England. Credit: Rob Pinney/Getty Images

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ ከ44 ቀናት በኋላ ስልጣናቨውን ለመልቀቅ ግድ ተሰኝተዋል። ይህም በእንግሊዝ ታሪክ ለአጭር ጊዜ በመሪነት የቆዩ መሪ አድርጓቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ከስልጣን እንደሚለቁ ለንጉሥ ቻርልስ ማስታወቃቸውን አካትተው ሁለት ደቂቃ ያልሞላ ንግግር አድርገው ከጋዜጠኞች ጥያቄ ሳይቀበሉ ወደ ቢሮአቸው ተመልሰዋል።

ተኪያቸውም በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በወግ አጥባቂው ፓርቲ እንደሚመረጥ ይጠበቃል።

ዛሬና ነገ ከወግ አጥባቂው ፓርቲ የምክር ቤት አባላት ውስጥ ሊዝ ትረስን ለመተካት ዕጩዎች ይቀርባሉ።

ይህም እንግሊዝ በአራት ወራት ውስጥ ሶስተኛ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሰየም ግድ ትሰኛለች።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now