'እናዝናለን' ዳታ የተጠለፈበት የጤና ኢንሹራንስ ኩባንያ ሜዲባንክ ደንበኞቹን ይቅርታ ጠየቀ

የዓለም ጤና ድርጅትና የሰብዓዊ መብቶች ተመልካች ድርጅት የሰሜን ኢትዮጵያ የግጭት መዘዞችን አስመልክተው ስጋታቸው ገለጡ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የመከላከያ ሠራዊት በደረሰባቸው የትግራይ ከተሞች ረድዔቶችን የሚያቀርብ የሰብዓዊ ድጋፍ ኮሚቴ አዋቅሮ ሥራ ማስጀመሩን አስታወቀ።

Medibank CEO David Koczkar offered an apology acknowledging the news would concern customers.jpg

Medibank CEO David Koczkar offered an apology acknowledging the news would concern customers. Credit: AAP / JULIAN SMITH/AAPIMAGE

የጤና ኢንሹራንስ ድርጅቱ ሜዲባንክ ከተጠርጣሪ ዳታ ጠላፊ ቡድን የደረሰውን መልዕክት ተከትሎ ደምበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል።

የኢንሹራንስ ኩባንያው ከፌዴራል መንግሥቱ የሳይበር ደኅንነት ኤጂንሲዎች ጋር በመተባበር የተጠለፉበትን የደንበኞቹን ዳታ አስመልክቶ ብርቱ ምርመራ እያካሔደ መሆኑን ገልጧል።

የሳይበር ደኅንነት ሚኒስትር ክሌየር ኦኒል የአውስትራሊያ ኩባንያዎች የደምበኞችን ዳታ ጠብቆ ለመያዝ አሁን እያደረጉ ካሉት ጥረቶች የበለጠ ታካይ ጥረቶችን ማድረግ እንደሚገባቸው አሳበዋል።

ከጥቂት ሳምንታት በፊትም የአውስትራሊያ ሁለተኛው ግዙፍ የቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያ ኦፕተስ ደንበኞች መሰረቁ ይታወሳል።

ሰሜን ኢትዮጵያ

በሰሜን ኢትዮጵያ በኢትዮጵያና መንግሥትና ሕወሓት መካከል እየተካሔደ ያለውን ግጭት አስመልክቶ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ስላስከተላቸውና የሚያስከትላቸውን የጤና ቀውሶች አስመልክተው ስጋታቸውን ገልጠዋል።

አክለውም፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለቀውሱ ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጥ አበረታተዋል። የዘር ማጥፋት እንዳይደርስም ጠባብ መስኮት ነው ሲሉ አመላክተዋል።

በሌላም በኩል የሰብዓዊ መብቶች ተመልካች (HRW) ኦክቶበር 18 ባወጣው መግለጫ በመንግሥት ቁጥጥር ስር በገባችው ሽሬ ከተማ ባሉት ሰዎች ላይ እንደ ከዚህ ቀደሙ በኢትዮጵያና ኤርትራ ጦሮች የግድያና ሰቆቃ ተግባራት እንዳይፈፀሙ ስጋት አለኝ ብሏል።

አያይዞም፤ የትግራይ ተዋጊዎችም በአማራ ክልል ቆቦ ከተማ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ግድያ መፈፀማቸውንና የንብረት ውድመቶችን ማድረሳቸውን አመልክቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ከሕወሓት እጅ አውጥቶ በራሱ ቁጥጥር ስር ባደረጋቸውና በሚያደጋቸው ከተሞች ሰብዓዊ እርዳታዎች ቀልጥፈውና ተሳልጠው እርዳታ ለሚሹ ወገኖች እንዲደርሱ የሚያስችል አንድ አስተባባሪ ኮሚቴ ማቋቋሙንና ሥራውንም እንደጀመረ አስታውቋል።

ኮሚቴው የተዋቀረው ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ ከአገር መከላከያ ሠራዊት፣ ፌደራል ፖሊስና የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ተውጣጥቶ ነው።

የኮሚቴው ሰብሳቢ ሆነው የተመደቡት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሲሆኑ፤ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦቱ የሽሬ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ እንደሚካሔድ ገልጠዋል።

ይህንኑ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና መሠረታዊ አገልግሎቶችን የማስቀጠል ትልምና ሂደትን አስመልክቶ የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥቅምት 8 ቀን 2015 ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ሰሞኑን ከመቀሌ ሰሜናዊ ምዕራብ 140 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውን ሽሬ ከተማን፣ እንዲሁም ከመቀሌ 170 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያለችውን ኮረምንና በ180 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኘውን አላማጣን በቁጥጥሩ ስር እንዳደረገ አመልክቷል። .

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
'እናዝናለን' ዳታ የተጠለፈበት የጤና ኢንሹራንስ ኩባንያ ሜዲባንክ ደንበኞቹን ይቅርታ ጠየቀ | SBS Amharic