በአፍሪካ ቀንድ እስከ 20 ሚሊየን ሰዎች በ2022 ሊራቡ እንደሚችሉ የዓለም ምግብ ፕሮግራም አመለከተ

*** 7.2 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም

News

Aid distribution. Source: Getty

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ ከሰብዓዊ እርዳታ እጥረት ጋር ታክሎ በዝናብ መዘግየት ሳቢያ በሚፈጠረው ብርቱ ድርቅ በዚህ ዓመት እስከ 20 ሚሊየን የአፍሪካ ቀንድ ሰዎች ሊራቡ እንደሚችል አስታወቀ። 

የዓለም ምግብ ፕሮግራም አያይዞም ሶማሊያ በመጪዎቹ ስድስትወራት ውስጥ ለረሃብ እንደምትጋለጥ፣ 7.2 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ከወዲሁ በቂ ምግብ እያገኙ እንዳልሆነና ኬንያም በእጅጉ ለከፋ ረሃብና የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንደምትጋለጥ አመላክቷል። 

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሶስት ሚሊየን ያህል የቀንድ ከብቶች ለሞት መዳረጋቸውም ተገልጧል።  

የተመድ ሰብዓዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ኤጄንሲ በበኩሉ ምንም እንኳ ወደ አፋርና ትግራይ የረድዔት አቅርቦቶች ሁኔታ መሻሻል ቢያሳዩም በገደቦችና ግጭቶች ሳቢያ ሰሜናዊ የኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ ረድዔቶችን ለማዳረስ አዋኪ መሆኑን ጠቅሷል። 

ኤጀንሲው በትግራይ ምሥራቃዊ ዞን የምትገኘው ኢሮብ ወረዳ ከ33 ሺህ በላይ ሰዎች (65 ፐርሰንት ያህል የወረዳዋ ነዋሪዎች) ውስን እርዳታ ብቻ ማግኘታቸውንና ለብርቱ የምግብ ዋስትና እጦት መጋለጣቸውንም አመልክቷል። 

አያይዞም፤ በአማራ ክልል የረድዔት ተደራሽነት ቢሻሻልም በሰሜን ጎንደር፣ ዋግኽምራና ሰሜን ወሎ ዞኖች ተደራሽነቱ አዋኪ ስለመሆኑ ተገልጧል።

የአካባቢውን መንግሥት አኃዝ የጠቀሰው ሪፖርት ከጃኑዋሪ 2022 አንስቶ በዋግኽምራ ዞን 61,000 እንዲሁም በሰሜናዊ ወሎ ዞን ከ57,000 በላይ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መኖራቸውን አስፍሯል።

በተጨማሪም ከ51,000 በላይ ሰዎች በውስጣዊ ውጥረቶች ሳቢያ ከኦሮሚያ ክልል ወደ አማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ተፈናቅለው መሔዳቸውን ጠቁሟል።


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service