የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ ለአውስትራሊያ - ቻይና ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ቢጂንግ ገቡ

ቻይና የአውስትራሊያን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባለፉት አራት ዓመታት ጊዜያት ውስጥ ወደ ቤጂንግ ለዲፕሎማሲያዊ ንግግር ስትጋብዝ ይህ የመጀመሪያ ሲሆን፤ የአውስትራሊያና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተመሠረተበት 50ኛ ዓመት ጋርም የተገጣጠመ ነው።

FM Penny Wong.jpg

Australian Foreign Affairs Minister Penny Wong arrives in Beijing, China, Tuesday, December 20, 2022. Credit: AAP Image/Lukas Coch

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዎንግ ቻይና የገቡት በቤጂንግ ሰዓት አቆጣጠር ማክሰኞ 10.38pm በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር ረቡዕ 1.38am AEDT ነው።

ሚኒስትር ዎንግ ቤጂንግ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሱ በቻይና የአውስትራሊያ አምባሳደር ግራሃም ፍሌቸር አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ከቻይናው አቻቸው ዋንግ ዪ ጋር ተገናኝተው ሲነጋገሩ፤ ቻይና በዓመት ከ200 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ በሚያስገኙ በተለያዩ የአውስትራሊያ ምርቶች ላይ የጣለችቻቸው ማዕቀቦች ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሚሆን ይጠበቃል።

በታካይነትም አውስትራሊያዊቷን ጋዜጠኛ ቼንግ ሊይን ጨምሮ ቻይና ውስጥ በእሥር ላይ የሚገኙ አውስትራሊያውያን ጉዳይም እንደሚነሳ ይታመናል።

ሴናተር ዎንግ ቻይና እንደገቡ ከቤጂንግ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከረጅም ዓመታት በኋላ ቻይና መገኘታቸው ማለፊያ እንደሆነ ጠቅሰው" የሁለቱን አገራት 50ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማክበር እንዲያስችል እዚህ በመገኘቴ ለቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ዕውቅናና ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል።

አያይዘውም፤ የጉብኝታቸው አንዱ ስኬት ንግግሩ እራሱ መሆኑን ልብ አሰኝተው፤ በርካታ ዕልባት ሊበጅላቸው የሚሹ ጉዳዮም እንዳሉ አመላክተዋል።



Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ ለአውስትራሊያ - ቻይና ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ቢጂንግ ገቡ | SBS Amharic