ክሪስ ሂፕኪንስ ተቀናቃኝ አልባ ሆነው ነገ አዲሱ የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ ነው

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልበኒዚ ከማይክሮሶፍት መሥራቹ ቢሊየነር ቢል ጌትስ ጋር ኪሪቢሊ ሃውስ ተገናኝተው በአየር ንብረት ለውጥ፣ የኃይል ምንጭና የጤና ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

Chris Hipkins, New Zealand's incoming prime minister.jpg

Chris Hipkins, New Zealand's incoming prime minister, during a news conference outside Parliament in Wellington, New Zealand, on Saturday, Jan. 21, 2023. Hipkins is set to succeed Jacinda Ardern as New Zealand's prime minister after the ruling Labour Party said he is the only nominee to be its next leader. Credit: Mark Coote/Bloomberg via Getty Images

የ37 ዓመቷን የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አደርን ከኃላፊነትን በራሳቸው ፈቃድ መልቀቅን ተከትሎ፤ የ44 ዓመቱ የትምህርትና ፖሊስ ሚኒስትር ክሪስ ሂፕኪንስ በነገው ዕለት የጠቅላይ ሚኒስትር በትረ መንግሥትን ሊጨብጡ ነው።

ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ዕጩ ሆኖ ለመቅረብ ለሚሹ የኒውዝላንድ ሌበር ፓርቲ ምክር ቤት አባላት እስከ ዛሬ ጠዋት ሶስት ሰዓት በተቆረጠው ቀነ ገደብ ከክሪስ ሂፕኪንስ በስተቀር የቀረበ ዕጩ ባለመኖሩና የፓርቲያቸው ድጋፍም የተቸራቸው በመሆኑ በነገው ዕለት አዲሱ የኒውዝላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሐላ ይፈፅማሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አደርንም ሙሉ በሙሉ ኃላፊነታቸውን አስረክበው ከስልጣናቸው ይሰናበታሉ።

የሂፕኪንስን ተተኪ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆንን አስመልክቶ በቀዳሚነት የ"እንኳን ደስ ያለዎት" መልዕክት ያስተላልፉት የአውስትራሊያው ሌበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሆኑ፤ ከሂፕኪንሰን ጋር በስልክ ተነጋግረዋል።

በመጪዎቹ ጊዜያትም አብረዋቸው ለመሥራት እንደሚሹ ያላቸውን ፍላጎት ገልጠዋል።
አልበኒዚ - ጌትስ

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልበኒዚ ዛሬ ቅዳሜ ጃኑዋሪ 21 ኪሪቢሊ ሃውስ ከማክሮሶፍት መሥራቹ ቢል ጌትስ ጋር ተገናኝተው yeአየር ንብረት ለውጥ፣ የኃይል ምንጭና የጤና ጉዳዮችን አንስተው ተወያይተዋል።
አቶ ጌትስ አውስትራሊያን እየጎበኙ ያሉት ከጌትስ ፋውንዴሽንና በቴክኖሎጂ የአየር ብክለትን ለመቀነስ፣ ዘላቂና አስተማማኝ የኃይል ምንጭ ለማበርከት ተነሳሽነት ወስዶ ካለው ብሬክስሩ ኢነርጂ ኩባንያ ተወካዮች ጋር በመሆን ነው።

የማይክሮሶፍት መሥራቹ የወባ በሽታን ከሪጂኑ ለማጥፋት ከአውስትራሊያ ጋር በሽርካነት እየሠሩ ይገኛሉ።

 



 


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service