ፕሬዚደንት ዜለንስኪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዩክሬይንን እንዲጎበኙ ጋበዙ

አውስትራሊያ አየርላንድ ሪፐብሊክን በሴቶች እግር ኳስ የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ግጥሚያ 1 - 0 ረታች፤ ናይጄሪያና ካናዳ 0 - 0 ተለያዩ።

gettyimages-1529218622-612x612.jpg

President of Ukraine, Volodymyr Zelenskyy, speaks at the press conference during NATO Summit at LITEXPO Lithuanian Exhibition and Congress Center in Vilnius, Lithuania, on July 12, 2023. Credit: NurPhoto/NurPhoto via Getty Images

የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቮሎድሚር ዜለንስኪና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሁለቱ አገራት ግንኙነት ለመጀመሪያ ጊዜ የሆነ የስልክ ንግግር አድርገዋል።

ንግግራቸው ያተኮረውም የሩስያ ከጥቁር ባሕር የእህል አቅርቦት ተነሳሽነት መውጣት፣ የባሕር ቀዘፋን መግታት፣ የዩክሬይን ወደብና የኃይል መሠረተ ልማት ላይ የቦምብ ድብደባ ማካሔድ ላይ እንደነበር የዩክሬይን ፕሬዚደንታዊ ጽሕፈት ቤት ገልጧል።

አቶ ዜሌንስኪ፤ በስልክ ንግግሩ ወቅት በዩክሬይንና በአፍሪካ አገራት መካከል የንግግር መድረኮችን መፍጠር እንደሚያሻ ያነሱት ሲሆን፤ አያይዘውም "የኢትዮጵያ ድምፅ፣ የአፍሪካ ሕብረት ድምፅ፣ የመላው አፍሪካ ድምፅ ለእኛ ጠቃሚ ነው" ብለዋል።

ሁለቱ መሪዎች ሉላዊ የሰላም ጉባኤ በማዘጋጀት ላይ እንደመከሩና ፕሬዚደንት ዜለንስሊ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዩክሬይንን እንዲጎበኙ የጋበዙ መሆኑን የፕሬዚደንቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

የዓለም ዋንጫ

ትናንት በአውስትራሊያና ኒውዝላንድ የጋራ አስተናጋጅነት ሲድኒ ላይ በተካሔደው የሴቶች ዓለም ዋንጫ መክፈቻ ግጥሚያ አውስትራሊያ አየርላንድን በፍፁም ቅጣት ምት በተገኘች ግብ 1 - 0 ስታሸንፍ ኒውዝላንድ ኦክላንድ በተደረገው ግጥሚያ ኖርዌይን በተመሳሳይ ውጤት 1 - 0 ረታለች።
Steph Catley of Australia.jpg
Steph Catley of Australia (centre) celebrates with teammates after scoring a penalty during their opening match of the 2023 FIFA Women's World Cup against Ireland in Sydney on Thursday night. Credit: AAP / Dan Himbrechts

የአውስትራሊያ ቀጣዩን ግጥሚያ ከናይጄሪያ ጋር ብሪስበን ላይ ሐሙስ ጁላይ 27 / ሐምሌ 20 ታካሂዳለች።





Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ፕሬዚደንት ዜለንስኪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዩክሬይንን እንዲጎበኙ ጋበዙ | SBS Amharic