"የተባበሩት መንግሥታት ፀጥታ ምክር ቤት ረብ የለሽና ኢ-ዲሞክራሲያዊ ነው" የኬንያ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ

ካናዳ ሕንድን በዜጋዋ ግድያ እጇ አለበት ስትል በአደባባይ ከሰሰች፤ ሕንድ ለካናዳ ዜጎች ቪዛ መስጠት አቆመች

President of Kenya William Samoei Ruto

President of Kenya William Samoei Ruto speaks during the United Nations General Assembly (UNGA) at United Nations headquarters on September 21, 2023, in New York City. Credit: Kena Betancur/Getty Images

የኬንያ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ መድረክ ላይ ተገኝተው የተመድ ፀጥታ ምክር ቤትን ረብ የለሽና ኢ-ዲሞክራሲያዊ ሲሉ ተናገሩ።

አቶ ሩቶ በንግግራቸው ወቅት የሄይቲን ጉዳይ ነቅሰው በማንሳት፤ የተባበሩት መንግሥታት ሄይቲን ገጥመዋት ላሉት ተግዳሮቶች ትድግና አስቸኳይ ፍኖተ ካርታ ዘርግቶ ሕብረ ብሔራዊ ፀጥታ አስከባሪ ኃይል ድጋፍ እንዲልክም አሳስበዋል።

የኬንያው ፕሬዚደንት የዓለም አቀፍ ፋይናንስ ተቋማትን አስመልክተው የተናገሩ ሲሆን፤ አክለውም፤

"የተባበሩት መንግሥታት ፀጥታው ምክር ቤት ረብ የለሽ፣ ኢ-ዲሞክራሲያዊ፣ አካታች ያልሆነ፣ ሁሉን አቀፍ ውክልና የለሽ ስለመሆኑ ማረጋገጫ የሚሻ ካለ፤ በእዚያ ሳቢያ በዓለማችን ላይ በአሁኑ ወቅት ተንሰራፍቶ ያለው የተወሰኑ ተዋንያን ተጠያቂነት ሳያገኛቸው የሉላዊ ጉዳዮች መከወን ነው" ብለዋል።

ካናዳና ሕንድ

የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ካናዳ ውስጥ በተፈፀመው የሲክ ተገንጣይ ቡድን መሪ ሃርዲፕ ሲንግ ኒጃር ግድያ የሕንድ እጅ እንዳለበት ፍንጮች መኖራቸውን ዳግም አንስተው ተናግረዋል።

ኒጃር ሕንድ ውስጥ "አሸባሪ" ካናዳ ውስጥ በ"ሃይማኖት መሪነት" ይታወቃሉ።

ሕንድ በአሸባሪነት ከመፈረጅም አልፋ ለእስር ለመዳረግ አቶ ኒጃር የት እንደሚገኙ ለጠቆመ 1 ሚሊየን ሩፒ ወይም 9,710 ፓውንድ ወሮታ ለመክፈል ማስታወቂያ አውጥታለች።

የአቶ ኒጃር ሕይወት ካናዳ ውስጥ ያለፈው ጁን 18 ሁለት ጭምብል ባጠለቁ ግለስቦች እጅ ነው።

አቶ ትሩዶ የሕንድን በሕንዳዊው ካናዳዊ ዜጋ ግድያ እጇ የለባት ስለመሆኑ መንግሥታቸውን ያለውን መረጃ እስካሁን ያላቀረቡ ቢሆንም፤ የሕንድ መንግሥት ግድያውን አስመልክቶ እውነት ላይ የተመሰረተ ዕልባት ለማበጀት ከካናዳ ጋር ሊነጋገር እንደሚገባ አሳስበዋል።

 ሕንድ በሁለቱ አገራት መካክለ ያለው ልዩነት እየሰፋ መሔድን ተከትላ ለካናዳ ዜጎች ቪዛ መስጠትን ገትታለች፤ እንዲሁም ወደ ካናዳ ለሚሔዱ ዜጎቿ በተለይም ተማሪዎች ደህንነታቸውን ነቅተው እንዲጠብቁ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አውጥታለች።










Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service