ቻይናና ሩስያ ግንኙነታቸውን ሲያጠናክሩ፤ዩናይድ ስቴትስ የኔቶ "ግንባር መስመር" ምሥራቃዊ አባል አገራትን እያበረታታች ነው

የቻይናው ፕሪዚደንት ሺ ዓርብ ዕለት "የሰላም ንግግር" የሚያደርጉ ሲሆን፤ የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቭላድሚር ዜሌንስኪ የሩስያ ወታደሮች የዩክሬይንን ምድር ለቅቀው እስካልወጡ ድረስ ስለ ሰላም ንግግር ማንሳት ከንቱ መሆኑን አስታወቁ።

Russian President Vladimir Putin meets with China's Director of the Office of the Central Foreign Affairs Commission Wang Yi .jpg

Russian President Vladimir Putin meets with China's Director of the Office of the Central Foreign Affairs Commission, Wang Yi, at the Kremlin in Moscow. Credit: Getty / Anton Novoderezhkin

የቻይና ከፍተኛ ዲፕሎማት ዋንግ ዪ የደህንነት ጉዳይን አስመልክተው ከሩስያ ጋር ለመነጋገር እንደሚሹ ለሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ገልጠዋል።

አቶ ዋንግ ከሩስያው ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል።
 
የዲፕሎማቱ የሩስያ ጉብኝት የተካሔደው የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ቻይና ለሩስያ የዩክሬይን ወረራ የቁሳቁስ ድጋፍ እንዳታደርግ ማሳሰቢያ መስጠትን ተከትሎ ነው።  

ይሁንና አቶ ዋንግ የቻይና-ሩስያ ግንኙነት "እጅግ ጠንካራና እየተለወጠ በመሔድ ባለው ዓለም አቀፍ ሁኔታ ማናቸውንም ፈተና የሚቋቋም ነው" ብለዋል።

 በሌላ በኩል የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ሩስያ ዩክሬይንን የወረረችበትን አንደኛ ዓመት በማንሳት ተከስቶ ያለውን ሉላዊ ውጥረት በማመላከት ለኔቶ "የግንባር መስመር" ምሥራቃዊ አባል አገራት የደህንነት ማረጋገጫ ቃል ሰጥተዋል።

የቻይናው ፕሬዚደንት ሺ ሞስኮ ዘልቀው ከሩስያው አቻቸው ጋር የሚገናኙ ሲሆን፤ ዓርብ ዕለት "የሰላም ንግግር" ያደርጋሉ።

ሆኖም፤ የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቭላድሚር ዜሌንስኪ የሩስያ ወታደሮች የዩክሬይን ምድርን ለቅቀው እስካልወጡ ድረስ ከሩስያ ጋር የሰላም ንግግር ለማድረግ እንደማይፈቅዱ አስታውቀዋል።








Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service