Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ኢትዮጵያ የብሪክስ ሙሉ አባል ሆነች

በደቡብ አፍሪካ የተካሔደው 15ኛው የብሪክስ ጉባኤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ስድስት አገራትን በሙሉ አባልነት ተቀበለ።

BRICS Summit 2023

Luiz Inacio Lula da Silva, Brazil's president, Xi Jinping, China's president, Cyril Ramaphosa, South Africa's president, Narendra Modi, India's prime minister, and Sergei Lavrov, Russia's foreign minister, left to right, on the closing day of the BRICS summit at the Sandton Convention Center in the Sandton district of Johannesburg, South Africa, on Thursday, Aug. 24, 2023. Credit: Bloomberg/Bloomberg via Getty Images

ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነሐሴ 22 የተጀመረው የብሪክስ ጉባኤ ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ 18 የአባላቱን ቁጥር ለማስፋት ተስማምቶ ስድስት አገራትን በሙሉ አባልነት መቀበሉን አስታወቀ።

በሙሉ አባልነት የታከሉት አገራት ከአፍሪካ ኢትዮጵያና ግብፅ፣ ከደቡብ አሜሪካ አርጀንቲና፣ ከመካከለኛው ምሥራቅ ሳዑዲ አረቢያና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ መሆናቸውን የጉባኤው ሰብሳቢ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎሳ በይፋ አስታውቀዋል።

በአዲስ አባልነት ብሪክስን የተቀላቀሉትን አገራት የዋነኛ መሥራች አገራት መሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልካም ምኞት መግለጫ ንግግር አድርገዋል።

የ15ኛው ብሪክስ ጉባኤ አስተናጋጅዋ አገር ደቡብ አፍሪካ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎሳ የስድስቱ አገራት በሙሉ አባልነት መታከል የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነና በቀጣዩ ምዕራፍም ተጨማሪ አገራት እንደሚታከሉ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮም የኢትዮጵያን የብሪክስ ሙሉ አባልነት መብቃት አስመልክቶ ለመላው ኢትዮጵያውያን የ "እንኳን ደስ አላችሁ" መልዕክት አስተላልፏል።

አዲሶቹ የብሪክስ አባል አገራት ሙሉ የአባልነት ሥፍራቸውን ከጃኑዋሪ 1፣ 2024 ጀምሮ ይይዛሉ።

ቀጣዩ የብሪክስ ጉባኤ የሚካሔደው ሩስያ ውስጥ ሲሆን፤ ብሪክስ (BRICS) የሚለው ስያሜ የእንግሊዝኛ ምሕፃረ ቃል የ (Brazil, Russia, India, China እና South Africa) መገለጫ በመሆኑ ከአዲሶቹ ስድስት አገራት መታከል ጋር ተያይዞ የመጠሪያ ስያሜውን ይለውጥ እንደሁ ለጊዜው አልተገለጠም።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now