ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የሮቦዕዳ መርማሪ ሮያል ኮሚሽን መሰየሙን አስታወቁ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ ኢትዮጵያ ውስጥ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ ዜና "ጥልቅ ኃዘንና ድንጋጤ" የተሰማቸውን መሆኑን ገለጡ።

Albanese.jpg

(L-R) Attorney-General Mark Dreyfus, Australian Prime Minister Anthony Albanese, Minister for Social Services Amanda Rishworth, and Minister for the National Disability Insurance Scheme Bill Shorten speak to media during a press conference, in Sydney, Thursday, August 25, 2022. Credit: AAP Image/Bianca De Marchi

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በፌዴራል ምርጫ ዘመቻቸው ወቅት ፓርቲያቸው ቃል የገባውን የሮቦዕዳ ምርመራ ዕውን ለማድረግ የሮያል ኮሚሽን መሰየማቸውን አስታወቁ።

የሮቦዕዳ ባለፈው የሞሪሰን መንግሥት ወቅት በሺህዎች የሚቆጠሩ ድጎማ ተቀባዮች የሌለባቸውን የሴንተርሊንክ ዕዳ ባለዕዳ አድርጎ ያቀረበ ድርጊቱም በፍርድ ቤት ሕጋዊ አለመሆኑ በ2019 ተገልጧል።

በብይኑ መሠረትም የፌዴራል መንግሥቱ $1.9 ቢሊየን ዶላርስ የካሣ ክፍያ እንዲፈፅም ተደርጓል።

 አዲስ የተሰየመው ኮሚሽን ፕሮግራሙን ማቋቋም ለምን እንዳስፈለገ፣ ተጠያቂው ማን እንደሚሆን፣ አስፈላጊ የተባለበት ምክንያት ምን እንደሆነና መንግሥትን ያስወጣው ወጪ ዝርዝርን የሚመረምር ይሆናል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በንግግራቸው ወቅት "400 ሺህ ያህል አውስትራሊያውያን የዚህ ጨካኝ አሠራር ሰለባዎች መሆናቸውን እናውቃለን" ያሉ ሲሆን፤ አክለውም ኮሚሽኑ እንዲያ ያለ አሳፋሪ ተግባር ዳግም እንዳይፈፀም የሚሆንበትን ብልሃት እንዲያመልክትም ተጨማሪ ተግባር የተሰጠው መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህንኑ ተግባር ግብር ላይ ለማዋልም የፌዴራል መንግሥቱ የቀድሞዋን የኩዊንስላንድ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዋና ዳኛ ካትሪን ሆልምስን ሮያል ኮሚሽነር አድርጎ ሰይሟል።

***
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ ኢትዮጵያ ውስጥ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ ዜና "ጥልቅ ኃዘንና ድንጋጤ" የተሰማቸውን መሆኑን ገለጡ።

ዋና ፀሐፊው በመንግሥትና በሕወሓት መካከል በግጭት ፈንታ ወደ አስቸኳይ ተኩስ አቁምና የሰላም ንግግር እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።

ትናንት በኢትዮጵያ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በኩል በወጣው መግለጫ ሕወሓት ከለሊቱ 11 ሰዓት ላይ በምሥራቅ ግንባር በቢሶ በር፣ ዞብልና ተኩለሽ አቅጣጫዎች ጥቃት መክፈቱን አመልክቷል።

በሌላም በኩል ሕወሓት ወታደራዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ፤ ኦገስት 24 የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት 6ኛና 8ኛ እግረኛ ጦርና የ2ኛ፣ 6ኛ እና 8ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሮች በጮቤ በር፣ ጃኖራ፣ ጉባጋላ፣ ያለው፣ አላማጣ፣ ባላ እና ቢሶ በር አቅጣጫ ጥቃቶችን መሰነዘሩን ገልጧል።

ይህ በንዲህ እንዳለም፤ የተመድ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ሥራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር ዲቪ ቢዝሊ የሕወሓት ባለስልጣናት መቀሌ ከሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም 500 ሺህ ሊትር ነዳጅ አሰርቀዋል ሲሉ በቲዊተር ገፃቸው አስፍረዋል።

ድርጊቱንም በአሳፋሪነት ገልጠው፤ የተወሰደው ነዳጅ በአስቸኳይ እንዲመለስ ጠይቀዋል።








 





Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የሮቦዕዳ መርማሪ ሮያል ኮሚሽን መሰየሙን አስታወቁ | SBS Amharic