Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

'ዕለቱ የስጦታ ነው'የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በገና በዓል መልዕክታቸው የልገሳ ጥሪና ምስጋና አቀረቡ

አውስትራሊያውያን የኮቪድ - 19 ገደቦች ከተነሱ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ላይ ተሰባስበው ዕለተ ገናን በሚያከብሩበት ወቅት አዲሶቹ መሪዎች አንቶኒ አልባኒዚ በጠቅላይ ሚኒስትርነት፣ ፒተር ዳተን በተቃዋሚ ቡድን መሪነት የመጀመሪያ የመልካም ምኞትና ምስጋና መልዕክቶቻቸውን አቅርበዋል።

PM Anthony Albanese.jpg

Prime Minister Anthony Albanese has thanked emergency service and defence personnel in his first Christmas message as prime minister.

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የገናን በዓል አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር "ከቤተሰብና ከወዳጆች ጋር በጋራ ዘና መባያ" እና ለበርካታ አውስትራሊያውን "የዕምነት ማዕከል" መሆኑንም አመላክተዋል።

አክለውም፤ በዛሬዋ ዕለት በሥራ ገበታ፣ በበጎ ፈቃደኝነት፣ የድንገተኛ አደጋ ደራሽና በመከላከያ ግዳጅ ላይ ተሠማርተው ያሉ አውስትራሊያውያንን አስተዋፅዖዎች በማንሳት "ለአገልግሎቶቻቸሁ ምሥጋናዬንና አድንቆቴን አቀባለሁ" ብለዋል።

የፌዴራል ተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን በበኩላቸው 2022 በተፈጥሮ አደጋ ክስተት፣ በመጠነ ሰፊ ዳታ ስርቆትና በዳግማዊት ኤልሳቤጥ ሕልፈተ ሕይወት "እጅግ አዋኪ ዜና" አስቸጋሪ ዓመት እንደነበር አውስተዋል።

አያይዘውም፤ የኑሮ ውድነት አውስራሊያውያንን እየጎዳ መሔድ ላይ መሆኑን በመጥቀስ፤ በመጪዎቹ ወራትና ዓመታት የማኅበረሰባትንና መንግሥትን ድጋፎች ግድ እንደሚልም አመላክተዋል።

በዓለ ገናውንም አስመልክተው፤ ዘመድ አዝማድ አልባ አውስራሊያውያን በዓለ ገናን በብቸኝነት እንዳያከብሩ በክርስቲያን መንፈስ እንዲጎበኟቸውም አሳስበዋል።

እንዲሁም "ምንም እንኳ ዓመቱ አዋኪ የነበረም ቢሆን፤ በዓለ ገና ለአውስትራሊያውያን ምን ያህል ዕድለኞች እንደሆንንን፣ በዓለም ምርጥ በሆነች አገር የምንኖር መሆኑንም ዳግም የምንገልጥበት ነው" ሲሉ ተናግረዋል።


1 min read

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now