የማልከም-ኤክስ ሴት ልጅ ኤፍ.ቢ.አይ፣ ሲ.አይ.ኤ እና የኒውዮርክ ከተማ ፖሊስ ላይ ክስ ልትመሠርት ነው

የናይጄሪያ ፕሬዚደንታዊና የተወካዮች ምክር ቤት ብሔራዊ ምርጫ ይፋ ውጤት እስከ ማክሰኞ ይዘገያል።

Malcolm X.jpg

(Original Caption) 6/4/1963-Hartford, CT: Malcolm X, leading spokesman for the Black Muslim movement, is shown with the dome of the Connecticut Capitol behind him as he arrived in Hartford for a two day visit. Credit: Getty Images

 የሲቪል መብቶች ተሟጋች የነበሩት የማልከም-ኤክስ ሴት ልጅ የአባቷን አሟሟት አስመልክታ በኤፍ.ቢ.አይ፣ ሲ.አይ.ኤ እና የኒውዮርክ ከተማ ፖሊስ ላይ ክስ ልትመሠርት መነሳቷን አስታወቀች።

አፍሪካዊ - አሜሪካናዊው ማልከም ኤክስ እ.አ.አ. ፌብሪዋሪ 21,1965 ኒውዮርክ ከተማ ንግግር በማድረግ ላይ ሳሉ በ58 ዓመታቸው በጥይት ሕይወታቸው አልፏል።


በማልከም ኤክስ ግድያ በስህተት ተጠርጥረው የነበሩት መሐመድ አዚዝና ካሊል ኢስላም በ2021 ውነጀላቸው ተነስቶላቸዋል።


የማልከም ኤክስ ሴት ልጅ ኢልያሳህ ሻባዝ የአባታቸው ግድያ ከስለላና ሕግ አስከባሪ ድርጅቶች ጋር ተያይዥነት ስለመኖርና አለመኖሩ እውነታ እሳቸው፣ ቤተሰባቸውና ተከታዮቻቸው ማወቅ እንደሚሹ፣ የክስ ስሚውም ለጥያቄዎቻቸው ምላሾችን እንደሚያስገኙና ለአባታቸውም የሚገባቸውን ፍትህ ያስገኛል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናገረዋል።



 ጉዳዩን አስመልክቶ እስካሁን ከኤፍ.ቢ.አይ፣ ሲ.አይ.ኤ እና የኒውዮርክ ከተማ ፖሊስ የተሰጠ ምላሽ የለም።



የናይጄሪያ ብሔራዊ ምርጫ 2023

በአማፂ እስላማዊ ቡድናት፣ እገታ፣ ግጭት እያመሳትና፣ የጥሬ ገንዘብ፣ ነዳጅና የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት፣ ስር የሰደደ ሙስናና ድህነት አውኳት ያለችው ናይጄሪያ መራጮች ለአገር አቀፉ ምርጫ ድምፆቻቸውን ሰጥተዋል።

ይሁንና በርካታ መራጮች በተጓተተው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ መራጮችን መስፈራራትና ቴክኒካዊ እክሎችን አስመልክተው ብስጭታቸውን ገልጠዋል።
 
ለስምንት ዓመታት ስልጣን ላይ ቆየተው ተሰናባች የሆኑትን የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ማሃማዱ ቡሃሪን በአዲስ ፕሬዚደንት ለመተካትና የተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ለመምረጥ የተከናወነው ብሔራዊ ምርጫ ውጤት ተጠቃሎ ይፋ ለመሆን እስከ ማክሰኞ የቆጠራ ጊዜን ግድ እንደሚል ተነግሯል።
 






 


Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service