የቡድን 20 ሚኒስትሮች የዩክሬይንን ጦርነት በአንድ ድምፅ በመግለጥ ላይ ሳይስማሙ ቀሩ።
የዓለም ግዙፍ የምጣኔ ሃብት አገራት ሚኒስትሮች ስብሰባ የተካሔደው በሕንድ አስተናጋጅነት ሲሆን፤ ከሩስያና ቻይና በገጠመው ተቃውሞ ሳቢያ ከስምምነት ላይ መድረስ ሳይችል ቀርቶ አክትሟል።
ባለፈው ወርኃ ኖቬምበር ባሊ-ኢንዶኔዥያ የተካሔደው የቡድን 20 የመሪዎች ስብሰባ ግጭቱ በውዥቀት ላይ ያለውን የዓለም ምጣኔ ሃብት ለባሰ ሁኔታ ሊዳርግ እንደሚችል በማሳሰብ በብርቱ አውግዞ ነበር።
ይሁንና የሕንድ ፋይናንስ ሚኒስትር ኒርማላ ሲታራማን በአሁኑ ወቅት ከጋራ ስምምነት ላይ የደረሰ መግለጫ ማውጣት እንደማይቻል አመላክተው፤ በምትኩ የጉባኤው ሰብሳቢን ማጠቃለያና ከጋራ ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልተቻለ የሚያመላክት ሰነድን ይፋ ማድረግ አማራጭ ስለመሆኑ አስታውቀዋል።
የአውስትራሊያ ኤምባሲ በዩክሬይን
የአውስትራሊያ ፌዴራል ተቃዋሚ ቡድን አውስትራሊያ የኪየቭ ኤምባሲዋን ዳግም በመክፈቱ ላይ እንድታስብበት አሳሰበ።
የተቃዋሚ ቡድኑ ማሳሰቢያ መነሾ የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ከSBS የኤምባሲውን መዘጋት አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ፤ አውስትራሊያ የኪየቭ ኤምባሲዋን ዳግም በመክፈት ዲፕሎማሲያዊ ውክልናዋን እንድትቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ ነው።
I