የቡድን 20 ፋይናንስ ሚኒስትሮች የዩክሬይን ጦርነትን አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ለማውጣት ከስምምነት ላይ ሳይደርሱ ቀሩ

የዩክሬይን ፕሬዚደንት አውስትራሊያ ኤምባሲዋን ዳግም እንድትከፍት ጥሪ አቀረቡ

Ukrainian President Volodymyr Zelensky speaks to the media during a press conference in Kyiv.jpg

Ukrainian President Volodymyr Zelensky speaks to the media during a press conference in Kyiv. Credit: EPA / SERGEY DOLZHENKO/EPA

የቡድን 20 ሚኒስትሮች የዩክሬይንን ጦርነት በአንድ ድምፅ በመግለጥ ላይ ሳይስማሙ ቀሩ።

የዓለም ግዙፍ የምጣኔ ሃብት አገራት ሚኒስትሮች ስብሰባ የተካሔደው በሕንድ አስተናጋጅነት ሲሆን፤ ከሩስያና ቻይና በገጠመው ተቃውሞ ሳቢያ ከስምምነት ላይ መድረስ ሳይችል ቀርቶ አክትሟል።  

ባለፈው ወርኃ ኖቬምበር ባሊ-ኢንዶኔዥያ የተካሔደው የቡድን 20 የመሪዎች ስብሰባ ግጭቱ በውዥቀት ላይ ያለውን የዓለም ምጣኔ ሃብት ለባሰ ሁኔታ ሊዳርግ እንደሚችል በማሳሰብ በብርቱ አውግዞ ነበር።

ይሁንና የሕንድ ፋይናንስ ሚኒስትር ኒርማላ ሲታራማን በአሁኑ ወቅት ከጋራ ስምምነት ላይ የደረሰ መግለጫ ማውጣት እንደማይቻል አመላክተው፤ በምትኩ የጉባኤው ሰብሳቢን ማጠቃለያና ከጋራ ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልተቻለ የሚያመላክት ሰነድን ይፋ ማድረግ አማራጭ ስለመሆኑ አስታውቀዋል።  

የአውስትራሊያ ኤምባሲ በዩክሬይን

የአውስትራሊያ ፌዴራል ተቃዋሚ ቡድን አውስትራሊያ የኪየቭ ኤምባሲዋን ዳግም በመክፈቱ ላይ እንድታስብበት አሳሰበ።

የተቃዋሚ ቡድኑ ማሳሰቢያ መነሾ የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ከSBS የኤምባሲውን መዘጋት አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ፤ አውስትራሊያ የኪየቭ ኤምባሲዋን ዳግም በመክፈት ዲፕሎማሲያዊ ውክልናዋን እንድትቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ ነው።

 



 

I

Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service