በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሃደራ አበራ የሹመት ደብዳቤ አቀረቡ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ አኅጉር ያላት ሚና የላቀ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አውስትራሊያ ትኩረት ከምትሰጣቸው አገራት መካከል አንዷ መሆኗንና የኢትዮጵያ መንግሥት ኤምባሲውን በሙሉ አቅሙ ሥራ ማስጀመሩ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለው የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ ገለጡ።

Ambassador Hadera Abera.jpg

Ian McConville, Chief of Protocol for DFAT (L), and Hadera Abera Admassu, Ethiopian Ambassador to Australia (R). Credit: Embassy of Ethiopia, Canberra

በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርና ልዩ መልዕክተኛ ሃደራ አበራ አድማሱ ለአውስትራሊያ የንግድና ውጭ ጉዳይ ዲፓርትመንት የፕሮቶኮል ሹም ኢያን ማክኮንቪል ቅጂ የሹመት ደብዳቤያቸውን ሰኔ 19 ቀን 2015 ማቅረባቸውን በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።

አምባሳደር ሃደራ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅትም "በኢትዮጵያና አውስትራሊያ መካከል ላለፉት 60 ዓመታት የዘለቀውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር የኢትዮጵያ መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን፤ በማዕድንና ኢነርጂ፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉድኝት፣ በንግድ፣ በሙዋዕለ ንዋይ ፍሰት፣ በቱሪዝምና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፎች የሁለትዮሽ ግንኙነቶቹን ለማስፋት እንደሚሠሩ" መግለጣቸውን ኤምባሲው አመላክቷል።

አያይዞም "በሁለቱ አገራት መካከል እንደ ድልድይ ሆነው እያገለገሉ የሚገኙትን በአውስትራሊያ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ተሣትፎ የበለጠ በማጠናከር ዳያስፖራው በአገሩ ጉዳይና በሁለትዮሽ ግንኙነቱ የሚኖረው ሚና የጎላ እንዲሆን እንደሚሠሩ" መናገራቸውን አስታውቋል።

በአውስትራሊያ በኩል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፕሮቶኮል ሹም ማክኮንቪል "ኢትዮጵያ በአፍሪካ አኅጉር ያላት ሚና የላቀ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አውስትራሊያ ትኩረት ከምትሰጣቸው አገራት መካከል አንዷ መሆኗንና የኢትዮጵያ መንግሥት ኤምባሲውን በሙሉ አቅሙ ሥራ ማስጀመሩ የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ትልቅ ሚን የሚኖረው መሆኑን" እንደገለጡም ተመልክቷል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service