በቪክቶሪያ የክፍለ አገር መንግሥት ምርጫ ሌበር ፓርቲ ለሶስተኛ ጊዜ አብላጫ ወንበሮች ያሉት መንግሥት ለማቆም እየመራ ነው

የሌበር ፓርቲ ከምርጫ በፊት ከ88 የፓርላማ ምክር ቤት ወንበሮች 55ቱን አሸንፎ ይዞ የነበረ ሲሆን የሊብራልና ናሽናል ቅንጅት 27 ወንበሮች ነበሯቸው።

Victorian premier Daniel Andrews.jpg

Victorian premier Daniel Andrews. Credit: Darrian Traynor/Getty Images

የቪክቶሪያ ክፍለ አገራዊ የምርጫ ጣቢያዎች በመላው ቪክቶሪያ ዛሬ ማለዳ ላይ ከ 8am አንስቶ እስከ 6pm ለመራጮች ክፍት ሆነው ውለዋል።

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮች የሰጡት ድምፆች በቆጠራ ላይ ያሉ ሲሆን የተወዳዳሪ ፓርቲዎችና የግል ተመራጮች ውጤቶች በምርጫ ኮሚሽን አማካይነት እየተገለጡ ይገኛል።

 እንደ ABC የምርጫ ተንታኝ አንቶኒ ግሪን ገለጣ ሌበር ፓርቲ 50 ሊብራል / ናሽልስ 23 ግሪንስ ፓርቲ 5 የምክር ቤት ወንበሮችን አሸንፈዋል።

የሌበር ፓርቲ ከምርጫ በፊት ከ88 የፓርላማ ምክር ቤት ወንበሮች 55ቱን አሸንፎ ይዞ የነበረ ሲሆን የሊብራልና ናሽናል ቅንጅት 27 ወንበሮች ነበሯቸው።

አሸናፊ ፓርቲ ራሱን ችሎ መንግሥት ለማቆም የሚያስፈልጉት ወንበሮች 45 ናቸው።

ከጥቂት ደቂቃዎች ወይም ሰዓታት በኋላ የምርጫ ኮሚሽንን ይፋ ውጤት ተከትሎ ድል የተነሱት የሊብራል/ናሽናል ፓርቲ መሪ ማቲው ጋይ እና ይድል ባለቤት የሆኑት የሌበር ፓርቲ መሪ ዳን ኤል አንድሩስ ፓርቲዎቻቸውን ወክለው ንግግር ያደርጋሉ።






Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service