Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

"የመሰናበቻው ጊዜ አሁን ነው" የቪክቶሪያ ፕሪሚየር ዳንኤል አንድሩስ ከስልጣናቸው ለቀቁ

ዳንኤል አንድሩስ ለዘጠኝ ዓመታት ቪክቶሪያን ከመሩ በኋላ የፕሪሚየር ኃላፊነታቸውንና የማልግሬቭ የምክር ቤት አባልነታቸውን ጨምሮ ከነገ ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 5pm አንስቶ ይለቅቃሉ።

gettyimages-1263985252-612x612.jpg

Outgoing Premier of Victoria Daniel Andrews. Credit: Darrian Traynor/Getty Images

ዳንኤል አንድሩስ ለዘጠኝ ዓመትታ ቪክቶሪያን በ48ኛ ፕሪሚየርነት ማገልገል ታላቅ ክብር መሆኑን ገልጠው፤ የማልግሬቭ ምክር አባልነታቸውንም አክለው በፈቃዳቸው እንደሚለቅቁ ያስታወቁት ዛሬ ማክሰኞ ከቀትር በኋላ ነው።

ሁሌም "በቀላሉ ዝነኛ የሚያደርግ ላይ ሳይሆን፤ ሁሌም ትክክለኛ ለሆነ ተግባር በብርቱ መሥራት" ላይ አተኳሪ እንደነበሩ የገለጡት ፕሪሚየር አያይዘውም " የመሰናበቻውና ይህን ልዩና አስደማሚ ኃላፊነት ለሌላ ተረኛ አሳልፎ የመስጫው ጊዜ አሁን ነው" ሲሉ የስንብት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ዳንኤል አንድሩስን በፕሪሚየርነት የሚተኩት መሪ ነገ ከቀትር በኋላ በሌበር ፓርቲ ተመርጠው ኃላፊነቱን ይረከባሉ።

ዳንኤል አንድሩስ 48ኛው የቪክቶሪያ ፕሪሚየር ሆነው የተመረጡት ኖቬምበር 2014 ሲሆን በ2018 እና 2022 ለሶስት ጊዜያት በአብላጫ ድምፅ በቪክቶሪያ ነዋሪዎች ተመርጠዋል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now