ሱዳን ውስጥ የሞት ቁጥር እንደሚንር የዓለም ጤና ድርጅት አመለከተ

የተመድ ስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እንደገለጠው ወደ ቻድ ብቻ 270,000 ሱዳናውያን አገራቸውን ጥለው ለስደት ተዳርገዋል።

Sudan.jpg

A cloud of smoke rises after intense shelling and gunfights between soldiers and gunmen from the paramilitary Rapid Support Forces in Sudan on April 21, 2023, despite a three-day ceasefire north of Khartoum, Sudan. Credit: Omer Erdem/Anadolu Agency via Getty Images

በሱዳን መከላከያ ሠራዊትና በፈጣን ድጋፍ ኃይል ጦር መካከል በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ እስካሁን ሕይወታቸው ካለፈው በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በተጨማሪ አያሌዎች ለሞት ሊዳረጉ እንደሚችሉ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም አሳሰቡ።

ተዛማች በሽታዎች፣ የውኃና ምግብ እጥረት፣ የጤና አገልግሎትና ክትባት መቋረጥ ለተጨማሪ ሞት አስባብ እንደሚሆኑ ተገልጧል።

 በሁለቱ የሱዳን ጦሮች መከል ግጭት ከመቀስቀሱ በፊት የተባበሩት መንግሥታት 16 ሚሊየን ሱዳናውያን እርዳታ እንደሚሹ ጠቁሞ የነበረ ሲሆን፤ ግጭቱን ተከትሎ የእርዳታ ፈላጊ ሱዳናውያን ይበልጡን እንደሚያሻቅብ ተጠቅሷል።  

ዋና ዳይሬክተሩ እንዳመላከቱት፤ ፓራሚዲክስ፣ ነርሶችና ሐኪሞች የቆሰሉ ሰላማዊ ሰዎችን ቀርበው ለማከም እንዲሁም የሕክምና አገልግሎት መስጫዎች ዘንድም መድረስ እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።

አያይዘውም፤ ካርቱም ውስጥ ካሉት የጤና አገልግሎት ተቋማት ውስጥ 61 ፐርሰንቱ የተዘጉ ሲሆን፤ አዘቦታዊ የሕክምን አገልግሎቶቻቸውን መስጠት ላይ የሚገኙት 16 ፐርሰንት ብቻ መሆናቸውንም ገልጠዋል።

ከግጭቱ የሸሹ ሱዳናውያን ወደ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ግብፅ፣ ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን መዝለቃቸውን የተባብሩት መንግሥታት ምክትል ቃል አቀባይ ፋርሃን ሃቅ ተናግረዋል።

የተመድ ስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እንደገለጠው ወደ ቻድ ብቻ 270,000 ሱዳናውያን አገራቸውን ጥለው ለስደት መዳረጋቸውን ጠቅሷል።





Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ሱዳን ውስጥ የሞት ቁጥር እንደሚንር የዓለም ጤና ድርጅት አመለከተ | SBS Amharic