የኢትዮጵያ አየርመንገድ ከነገ አንስቶ የመቀሌ በረራውን ሊቀጥል ነው

ኢትዮ-ቴሌኮም በ27 የትግራይ ከተሞች አገልግሎቶቹን መስጠት ጀመረ

Ethiopian Airlines Airbus 350-900 .jpg

Ethiopian Airlines Airbus 350-900. Credit: Fabrizio Gandolfo/SOPA/mages/LightRocket via Getty Images

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ታህሳስ 19 አንስቶ በጦርነት ሳቢያ ተቋርጦ የነበረውን የመቀሌ በረራውን እንደሚጀምር የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አስታወቁ።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው ለአየር መንገዱ የበረራ ጅመራ አስባቡ በፌዴራል መንግሥቱና ሕወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት መርሃ ግብር ተከትሎ አመቺ ሁኔታ መፈጠሩ እንደሆነም አስረድተዋል።

በነገው ዕለት የሚያካሒደው በቀን የአንድ ጊዜ በረራ ሲሆን፤ የተጠቃሚዎች ቁጥር መጠን ከፍ ሲልም የበረራ አገልግሎቱ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጧል።

የቲኬት ሽያጭም ዛሬ ታሕሳስ 18 ቀን 2015 ጀምሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ወ/ሮ ፍሬሕይወት ታምሩ በበኩላቸው፤ በትግራይ 27 ከተሞች የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎቶች ዳግም ለተጠቃሚዎች እየተዳረሱ መሆኑን ተናግረዋል።

በጦርነቱ ሳቢያ ውድመት የደረሰባቸው የመሠረተ ልማት አውታሮች ጥገና እየተካሔደላቸው ይገኛል።

በሂደቱም 1,800 ኪሎ ሜትር የማያንስ የፋይበር ኦፕቲክ መስመር የጥገና ሥራዎች በመከናወን ላይ እንዳሉና እስካሁን የ931 ኪሎሜትር ጥገና ሥራዎች መጠናቀቃቸው ተመልክቷል።

በሌላም በኩል፤ የኤሌክትሪክና ባንክ አገልግሎቶችም ሥራ መጀመራቸውና ከሰሞኑም መጠነ ሰፊ አገልግሎት መስጠት እንደሚቀጥሉ ተነግሯል።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now