Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የሥራ ኃላፊነታቸውን እንደሚለቁ አስታወቁ

"ከነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነቴ በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን ለተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ጽሕፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ " ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ

Birtukan Mideksa NEBE.jpg

Birukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Credit: NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በገዛ ፈቀዳቸው ከኃላፊነት ለመልቀቅ በመወሰን መልቀቂያ ማቅረባቸውን አሳወቁ።

ብርቱካን ሚደቅሳ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት ከኃላፊነት ለመልቀቅ የወሰኑት በጤና ችግር ምክንያት ነው።

" ጤናዬን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልገኝ ሆኖ በመገኘቱ ከነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነቴ በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን ለተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ጽሕፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ " ብለዋል።

በሚቀራቸው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ስራዎችን የማጠናቀቅ እና አስተዳደራዊ ሽግግር የመፈፀም ሃላፊነቶችን እንደሚወጡም አስታውቀዋል።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now