የፌዴራል በጀት 2022/23 ይፋ ሆነ

*** የነዳጅ ቀረጥ ለስድሰት ወራት አሁን ካለው በሊትር 44 ሳንቲም በግማሽ ይቀንሳል። በአንድ ታንከር $15 ቁጠባ ያስገኛል፤ በጥቅሉ $3 ቢሊየን ወጪን ያስከትላል።

News

Australian Treasurer Josh Frydenberg hands down his fourth budget. Source: AAP

የፌዴራል በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ የ2022/23 በጀት ዛሬ ማምሻውን በፓርላማ ተገኝተው ይፋ አድረገዋል። 

በዚህ መሠረት፤

  • ለ10 ሚሊየን ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ገለሰቦች ከዚህ ዓመት ጁላይ 1 ጀምሮ የእንድ ጊዜ  1,500 ዶላርስ፣ ጥንዶች 3,000 የግብር ቅናሽ ያገኛሉ።
  • ለጡረተኞችና የቅናሽ ካርድ ተጠቃሚዎች $250 የአንድ ጊዜ የጥሬ ገንዘብ ክፍያ፤ በጥቅሉ $5.6 ቢሊየን ወጪን ያስከትላሉ።
  • የነዳጅ ቀረጥ ለስድሰት ወራት አሁን ካለው በሊትር 44 ሳንቲም በግማሽ ይቀንሳል። በአንድ ታንከር $15 ቁጠባ ያስገኛል፤ በጥቅሉ $3 ቢሊየን ወጪን ያስከትላል።
  • ጠቅላላ የአገሪቱ ዕዳ በ2023-24 ከአንድ ትሪሊየን ዶላር በላይ ያሻቅባል፤ በ2025-26 ወደ $1.17 ትሪሊየን ዶላር ወይም 44.7% ጠቅላላ የአገር ውስጥ ይንራል።
  • የሙዋዕለ ንዋይ ፍሰት ጉድለት በ2021-22 እስከ $79.8 ቢሊየን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
  • በቀጣይ አራት ዓመታት ውስጥ $224.7 ቢሊየን ሊደርስ ይችላል።
  • ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 4.25% በ 2021-22, 3.5% በ 2022-23 እና 2.5% በ 2023-24 ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።
  • የአውስትራሊያ ሥራ አጥነት መጠን በዚህ ዓመት የሴፕቴምበር ፋይናንስ ሩብ ዓመት ወደ 3.75% ዝቅ ይላል ተብሎ ይታሰባል። 
  • ለሜዲኬይር ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት 133 ቢሊየን ዶላርስ በጀት ውስጥ ገብቷል። 
  • 18 ሚሊየን ዶላርስ ለመድብለባህል ማሕበረሰባት የአዕምሮ ጤና ድጎማ ተመድቧል።
  • ለመከላከያ ለአሥር ዓመታት 270 ቢሊየን ዶላርስ ተበጅቷል። 

1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now