Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ኢርዶጋን ዳግም የተርኪዬ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ

ሜልበርን ጥንካሬው ከ120 ዓመታት በኋላ ብርቱ በተባለለት ርዕደ መሬት ተንጣ አደረች

President Recep Tayyip Erdogan.jpg

President Recep Tayyip Erdogan acknowledges supporters at the presidential palace after winning reelection in a runoff on May 29, 2023, in Ankara, Turkey. Erdogan was forced into a runoff when neither he nor his primary challenger, Kemal Kilicdaroglu of the Republican People's Party (CHP), received more than 50 per cent of the vote in the May 14 election. Credit: Chris McGrath/Getty Images

ሬሴፕ ጣይብ ኢርዶጋን ለተጨማሪ አምስት ዓመታት የተርኪዬ ፕሬዚደንት ሆነው ስልጣን ላይ የሚያቆያቸውን ዳግም ምርጫ በ 52.1 ፐርሰንት አሸነፉ።

አቶ ኤርዶጋን ከ2014 ጀምሮ ፕሬዚደንት፣ ቀደም ሲልም ለ11 ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣን ቆይተዋል። ተቀናቃኛቸው የተቃዋሚ ቡድን መሪ ከማል ኪሊችዳህሮህሉ 47.9 ፐርሰንት ድምፅ በማግኘት ድል ተነስተዋል።

የተቃዋሚ ቡድን መሪው ውጤቱን አልቀበለም ባይሉም ምርጫ ፍትሕዊ አልነበረም ብለው ሲያማርሩ፤ የፕሬዚደንት ኢርዶጋን ደጋፊዎች በጎዳናዎች ላይ በመደነስ ደስታቸውን ገልጠዋል።

የእርዶጋንን ዳግም መመረጥ አስመልክቶ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን፣ የሩስያ ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲንና የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚን ጨምሮ በርካታ የዓለም መሪዎች የመልካም ሥራ ዘመን ምኞት መግለጫዎቻቸውን ልከዋል።

ርዕደ መሬት

ሜልበርን ከ120 ዓመታት በኋላ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ገጥማት።

ከ 22,000 በላይ ሰዎች ጂኦሳይንስ አውስትራሊያ ዘንድ ደውለው የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተሰማቸው ገልጠዋል።

ትናንት እሑድ ሜይ 28 በሜልበርን ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 11:41 pm የተከሰተው ርዕደ መሬት ከሜልበርን አልፎ እስከ ሰሜናዊ ቤንዲጎ እና ደቡብ ሆባርት ድረስ ዘልቋል።

የርዕደ መሬቱ መጠን 3.8 ማግኒቲዩድ ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፤ እስካሁን በሳቢያው የደረሰ አደጋ አልተመዘገበም።

 


1 min read

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now