አል ሻባብ ሞቃዲሾ ውስጥ በአንድ ወር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ሰነዘረ

የሶማሊያ ፕሬዚደንት ሽብርን ከቀጣናው ለመክላት ሙሉ ዘመቻ እንደሚያካሂዱ አስታውቀዋል።

Somalian President Hassan Sheikh Mohamud.jpg

Somalian President Hassan Sheikh Mohamud. Credit: Murat Gok/Anadolu Agency via Getty Images

የትናንቱን ጥቃት አክሎ አል ሻባብ በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ለሁለተኛ ጊዜ በኦክቶበር ወር ውስጥ ጥቃት አድርሷል።

አል ሻባብ ባደረሰው ጥቃት አንድ ወታደርን ጨምሮ የስምንት ሰላማዊ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና አምስት ሰዎች ለመቁሰል አደጋ መዳረጋቸውን የፖሊስ ቃል አቀባይ ገሳዲቅ አሊ ገልጠዋል።

ቃል አቀባዩ አያይዘውም፤ 60 ሰዎችን ታግተው ከነበሩበት ሥፍራ መታደግ መቻሉንና 6 የአል ሻባብ ሚሊሺያዎችን መግደሉን አስታውቀዋል።

ጥቃቱ የደረሰው ሞቃዲሾ ቦንዲሂር ወረዳ በሚገኘውና በፖለቲከኞችና በበርካታ ተጠቃሚዎች በሚዘወተረው ቪላ ሮዛ ሆቴል ነው።

ጥቃቱን ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዚደንት ሐሰን ሼክ መሐመድ ከመከላከያ ሚኒስትራቸው ጋር ኪስማዩ ያለው ጦራቸው ዘንድ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ቀጣናውን ከአሸባሪዎች ለማፅዳት ለሙሉ ዘመቻ ዝግጁ እንዲሆኑ መናገራቸው ተገልጧል።

አል ሻባብ ባለፈው ወር በሁለት ፈንጂ የተጠመዱ ተሽከርካሪዎች ሞቃዲሾ ውስጥ በሰነዘረው ጥቃት 120 ያህል ሰዎች ለሞት ሲዳረጉ፤ በተመሳሳይ ሁኔታ ከአምስት ዓመት በፊት ከ500 በላይ ሰዎችን ሕይወት አጥፍቷል።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now