ዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ድርድር ላይ የተመሠረተ ተኩስ አቁም ስምምነት እንዲሰፍን ጥሪ አቀረበች

*** ሕወሓት ጦሬ ሙሉ በሙሉ አፋርን ለቅቆ ወጥቷል ሲል፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ሕወሓት ከአፋርና አማራ ክልሎች ጦሩን ጠቅልሎ እንዲወጣ ጠይቋል።

News

U.S. Secretary of State Antony Blinken. Source: Getty

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ኤፕሪል 29 ባወጡት መግለጫ በቅርቡ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት በኩል እየተወሰዱ ያሉ የጊዜያዊ ግጭት ማቆምና ሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦቶች አበረታች መሆናቸውን በማንሳት፤ በድርድር ላይ ወደ ተመሠረተ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመድረስ አጋጣሚውን እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል። 

አቶ ብሊንከን በሚሊየን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ለምግብ ዋስትና እጦትና ለረሃብ መጋለጥ መቀጠል የግጭቱ ቀጥተኛ ውጤት መሆኑን አመላክተዋል። 

በቅርብ ሳምንታት ውስጥም ለትግራይና አፋር ተጎጂ የማኅበረሰብ አባላት የረድዔት ምግብ ማቅረብ መቻሉ ያበረታታቸው መሆኑን አንስተው፤ ጥረቶቹንም በግጭቱ ለተጎዱ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ተደራሽነት እንዲኖር አክሎ ማስፋት እንዲቻል የኢትዮጵያ መንግሥትንና የክልሉን ባለስልጣናት እንደሚያበረታቱ ገልጠዋል። 

በቅርብ ወራት ውስጥም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ግጭቱ እንዲያበቃ፣ የአስቸኳይ ጊዜያዊ አዋጅ እንዲነሳ፣ የተወሰኑ የፖለቲካ እሥረኞችና ታጋቾ እንዲለቀቁ የማድረግ ተከታታይ የሆኑ አበረታች እርምጃዎች የወሰዱ መሆናቸውን አንስተዋል።

አያይዘውም፤ የትግራይ ባለስልጣናት የግጭት ማቆም እርምጃ ይፋ ማድረጋቸውንና አብዛኛዎቹም ኃይሎቻቸውንም ከአፋር በማስለቀቅ ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የማያመነቱ መሆናቸውን እንዳሳዩ ገልጠዋል። 

ሆኖም የአቶ ብሊንከንን መግለጫ ለማረም የሕወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ  የሕወሓት ጦር "ሙሉ በሙሉ" አፋርን ለቅቆ እንደወጣ ገልጠዋል።   

በተቃራኒው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሕወሓት "ከአፋርና አማራ ክልል አካባቢዎች እንዲወጣ" መንግሥት ጥሪ የሚያቀርብ መሆኑን በሚያዝያ 15 መግለጫው አስታውቋል።

 


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service