SKIP TO MAIN CONTENT

83ኛው የአገው ፈረሰኞች በዓል በዕንጅባራ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው

በበዓሉ ላይ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎች፣ የፈረስ ግልቢያ ትርኢቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየቀረቡ ነው።

Agaw 2023.jpg
Agaw Horse Riders' Festival 2023. Credit: PR

1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Skip to article content
ከዋናው የበዓሉ ቀን አስቀድሞ በነበሩት ቀናትም የቁንጅና ውድድር፣ ሩጫ፣ የቅኔ ምሽትና ሌሎችም ሁነቶች ተካሂደዋል።
የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎች እንዲሁም የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች በዓሉን እየታደሙ ይገኛሉ።
የአገው ፈረሰኞች በዓል በጣልያን ወረራ ወቅት ፈረሰኞች የፈፀሙትን ተጋድሎ ለመዘከር ከ83 ዓመታት በፊት የተመሰረተ ነው።
ማህበሩ አሁን ላይ ከ62 ሺህ በላይ አባላት ያሉት ሲሆን፤ የማህበሩ አባላት እርስ በርስ እንዲረዳዱ እና ማህበራዊ ጉዳዮችን በጋራ እንዲከውኑ እድል ፈጥሯል።
የአገውን ሕዝብ ባሕልና ማንነት በማስተዋወቅ ረገድም ማህበሩ የጎላ ሚና እየተጫወተ መሆኑ በበዓሉ ላይ ተገልጿል።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now