SKIP TO MAIN CONTENT

የኢትዮጵያ መንግሥትና የሕወሓት ጦር ገዲብ አዛዦች ዳግም ናይሮቢ ላይ ታደሙ

ስብሰባው የጋራ ቁጥጥር፣ ማጣራትና አከባበር ዘዴ ውል ማጣቀሻ ላይ ተወያይቶ ከማጠቃለያ ደርሷል። እንዲሁም፤ የትጥቅ ፍቺ፣ ብተናና ዳግም ቅልቅል ላይም ተነጋግሯል።

Commanders.jpg
The second meeting of the Senior Commanders of the Federal Democratic Republic of Ethiopia (FDRE) and the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) on December 22, 2022, in Nairobi, Kenya. Credit: AUC

1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Skip to article content

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በተሰየሙ የሰላም ልዑካን ቡድን እየተመራ ያለው የኢትዮጵያ መንግሥትና የሕወሓት ተደራዳሪዎች መካከል ቀጥሎ ያለው ቋሚ ከግጭት ዕቀባ ስምምነት ሂደት ትግበራ ክትትል ስብሰባ ዳግም ዲሴምበር 22/ ታሕሳስ 23 ናይሮቢ ከተማ ተካሂዷል።

ስብሰባው የጋራ ቁጥጥር፣ ማጣራትና አከባበር ዘዴ ውል ማጣቀሻ ላይ ተወያይቶ ከማጠቃለያ ደርሷል። እንዲሁም፤ የትጥቅ ፍቺ፣ ብተናና ዳግም ቅልቅል ላይም ተነጋግሯል።

የገዲብ አዛዦቹ ስብሰባ የተካሔደው በአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚደንት በሚመራው ልዑክ ቡድን ሲሆን፤ በዕለቱም የልዑካን ቡድን አባላቱ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ፉምዚሌ ምላምቦ ጉካ አማካይነት ነው።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now