አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትግራይ ውስጥ ወሲባዊ ጥቃቶች እንዲገቱ ለኢትዮጵያ መንግሥት ጥሪ አቀረበ

***አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ይፋ ባደረገው ሪፖርት የወሲባዊ ጥቃት ተሳትፎ አላቸው ያላቸውን የፀጥታ ኃይላትና ሚሊሺያ ቡድናትን ስም አስፍሯል

A detailed view of the Amnesty International logo. Getty

Source: Getty

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ኦገስት 11, 2021 ይፋ ባደረገው አዲስ ሪፖርት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ትስስሮሽ ባላቸው ኃይሎች ከትግራይ ግጭት ጋር ተያይዞ በመቶዎች በሚቆጠሩ ሴቶችና ልጃገረዶች ላይ ወሲባዊ ጥቃት መፈጸሙን ገልጧል።   

ሪፖርቱ በወሲባዊ ጥቃት ተሳታፊነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኃይል፣ የኤርትራ መከላከያ ኃይል፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ልዩ ኃይልና የፋኖ ሚሊሺያ ቡድንን በስም ጠቅሶ አስፍሯል።

ሪፖርቱ 63 ወሲባዊ ጥቃት ሰለባዎችንና የሕክምና ባለሙያዎችን ያነጋገረ መሆኑን የገለጠ ሲሆን፤ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዋና ፀሐፊ አግነስ ኮላማርድ በበኩላቸው "የኢትዮጵያ መንግሥት የፀጥታ ኃይላትና አጋር ሚሊሺያ አባላት ወሲባዊ ጥቃቶችን ከመፈጸም እንዲቆጠቡ አስቸኳይ እርምጃ መውሰድ አለበት፤ የአፍሪካ ኅብረት ያላንዳች ዝንፈት ግጭቱን ለአፍሪካ ኅብረት እና ፀጥታ ምክር ቤት ማቅረብ ይገባዋል" በማለት አሳስበዋል። 

የኢትዮጵያ መንግሥት በወሲባዊ አመፅ ተግባር ተሳትፈዋል ተብለው በተጠረጠሩ የመከላከያ አባላት ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ ቀደም ሲል ያስታወቀ ሲሆን በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በኩልም ምርመራ እየተካሔደ መሆኑ ተነግሯል።  

 

 

 


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትግራይ ውስጥ ወሲባዊ ጥቃቶች እንዲገቱ ለኢትዮጵያ መንግሥት ጥሪ አቀረበ | SBS Amharic